ከ«አልፋቤት» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
No edit summary
 
መስመር፡ 4፦
ከአልፋቤቶች ቀድሞ በሆነ ዘዴ በ«[[ሎጎግራም]]» ጽሕፈት እያንዳንዱ ምልክት ለተለየ ቃል ወይም ክፍለ-ቃል ይወክላል፣ ለምሳሌ [[የቻይና ጽሕፈት]] ዛሬም እንዲህ ነው። እንዲሁም «[[ሲላቢክ]]» በሚባለው መደብ፣ እያንዳንዱ ምልክት የተለየ ክፍለ-ቃል ድምጽ ያሰማል፣ ለምሳሌ የ[[ጻላጊኛ]] ጽሕፈት፣ ወይም እንደ [[አቡጊዳ]] ወይም እንደ [[ሕንድ]] [[ብራሚክ ጽሕፈቶች]] ቤተሠብ፣ የክፍለ-ቃል ድምጽ ምልክቶች እንደ አነንባቢው ተመሳሳይ ናቸው። ስለዚህ «አልፋቤቶች» እንደ «ሎጎግራም» ወይም «ሲላቢክ» ሳይሆኑ ከነዚህ ሁሉ የተለዩ ናቸው።
 
ከሁሉ አስቀድሞ የተደረጁት አልፋቤቶች ከ[[ቅድመ-ሴማዊ ጽሕፈት]] ሲሆኑ ለአናባቢዎቹ የተለዩ ምልክቶች አልነበራቸውም፣ ስለዚህ የነዚህ አልፋቤት አይነት «[[አብጃድ]]» ነው። [[የፊንቄ አብጃድ]]፣ [[የዕብራይስጥ አብጃድ]]፣ [[የአረብኛ አብጃድ]]፣ [[የአረማይስጥ አብጃድ]] ወዘተ. ሁላቸው በዚህ አይነት ናቸው። ስያሜው «አብጃድ» ከ[[አረብኛ]] መጀመርያ ፊደል ስሞች [[አ]]፣ [[በ]]፣ [[ጀ]]፣ [[ደ]] መጣ። ከነዚህም ብዙዎች እንደ ዕብራይስትናዕብራይስጥና አረብኛ አናባቢዎቹን በሌሎች ነጥቦች በኋላ አመለከቱ።
 
ምናልባት ከ800 ዓክልበ. ግድም ጀምሮ ግሪኮች የፊንቄ አብጃድ ትንሽ ቀይረው የአንዳንድ ድምጽ ጥቅም ከተነባቢ ወደ አናባቢ አዛወሩት። እነዚህ ከመጀመርያ [[የግሪክ አልፋቤት]] ፊደሎች ስሞች «[[አልፋ]]» እና «[[ቤታ]]» የተነሣ እውነተኛ «አልፋቤቶች» ይባላሉ። የአለም ዋና አልፋቤቶች በተለይም [[የላቲን አልፋቤት]]ና [[የቂርሎስ አልፋቤት]] ከዚያ ተደረጁ።