ከ«ባኃኢ እምነት» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
መስመር፡ 3፦
 
==ታሪክ==
የባሃይ ([[ፋርስኛ]]፦ /በሃኢ/ «የክብር») እምነት መነሻ ከ[[ሺዓ እስልምና]] ውስጥ ይቆጠራል። በሺዓ ውስጥ፣ እንዲሁም በፋርስ አገር ያብዛኞቹ ክፍል ውስጥ፣ «[[የአሥራሁለተኞቹ ወገን]]» ሲባሉ ይሄ ማለት የነቢዩ [[መሐመድ]] 12ኛው ተከታይ ወራሽ ወይም [[ኢማም]]፣ [[ሙሃመድ አል-ማህዲ]]፣ በ5ኛው አመተ እድሜ በ[[866]] ዓም ሳይሞት እንደ ተሰወረ፣ ወደፊትም በመጨረሻ ቀናት ለአለም ፍጻሜው ትግል፣ እርሱ ከ[[ኢሳ]] ([[ኢየሱስ]]) ጋር ይታያል የሚል የአብዛኞቹ ሺዓዎች ጽኑ እምነት ነው። ይህም እምነት በ[[እስልምና]] ትንቢቶች ላይ ይመሠረታል። «የ12ኞቹ ወገን» አማኞች እንግዲህ ከ866 ዓም ጀምረው ለዚሁ [[ማህዲ]] ዳግመና እንዲመልስ ጠብቀዋል።
 
በ[[1816]] ዓም በፋርስ፣ [[አህመድ ሻይኽ]] የተባለ መምህር የ[[ሻይኺስም]]ን እንቅስቃሴ መሠረተ፣ ይህም ወገን በተለይ የተነበየ ማህዲን ስለ ማግኘት ልዩ ትኩረት ይሰጥ ነበር። በሻይኽ አህመድ ተከታይ በ[[ሲዪድ ካዚም]] ዕረፍት በ[[1836]] ዓ.ም.፣ የሻይኺስም አማኞች በመላው ፋርስ ማህዲውን ለማግኘት ወጥተው፣ አንድ «ሲዪድ አሊ ሙሐመድ» የተባለ ወጣት አገኝተው «እኔ ለማህዲው መንፈሳዊው በር (ወይም [[ባብ]]) ነኝ» አላቸው። ሰውዬውም ከዚያ ጀምሮ «ባብ» በመባል ታውቀዋል፣ እንቅስቃሴውም «[[ባቢስም]]» ይባል ጀመር። ከትንሽ ጊዜ በኋላ ''ባብ'' እራሱ የተሠወረው ማህዲ እንደ ነበር ለተከታዮቹ አዋጀ፣ ከዚያም በኋላ ባብ «የአዲሱ ዘመን ነቢይ» በመጨረሻም «የአምላኩ ክስተት» መሆኑን በአዋጆች ገለጸ። ከዚህስ በኋላ የፋርስ ባለሥልጣናት ከ[[ቁርዓን]] በ[[ሺርክ]] እንደ ወጣ እንደ ረባሽ ወይም ሀረጤቃ ቆጥረውት አሠሩትና በ[[1842]] ዓም ይሙት በቃ ፈረዱበት።