ከ«ባኃኢ እምነት» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
Content deleted Content added
ጥ →ታሪክ |
|||
መስመር፡ 3፦
==ታሪክ==
የባሃይ እምነት መነሻ ከ[[ሺዓ እስልምና]] ውስጥ ይቆጠራል። በሺዓ ውስጥ፣ እንዲሁም በፋርስ አገር ያብዛኞቹ ክፍል ውስጥ፣ «[[የአሥራሁለተኞቹ ወገን]]» ሲባሉ ይሄ ማለት የነቢዩ [[
በ[[1816]] ዓም በፋርስ፣ [[አህመድ ሻይኽ]] የተባለ መምህር የ[[ሻይኺስም]]ን እንቅስቃሴ መሠረተ፣ ይህም ወገን በተለይ የተነበየ ማህዲን ስለ ማግኘት ልዩ ትኩረት ይሰጥ ነበር። በ[[1836]] ዓም የሻይኺስም አማኞች በመላው ፋርስ ማህዲውን ለማግኘት ወጥተው፣ አንድ «ሲዪድ አሊ ሙሐመድ» የተባለ ወጣት አገኝተው «እኔ ለማህዲው መንፈሳዊው በር (ወይም [[ባብ]]) ነኝ» አላቸው። ሰውዬውም ከዚያ ጀምሮ «ባብ» በመባል ታውቀዋል፣ እንቅስቃሴውም «[[ባቢስም]]» ይባል ጀመር። ከትንሽ ጊዜ በኋላ ''ባብ'' እራሱ የተሠወረው ማህዲ እንደ ነበር ለተከታዮቹ አዋጀ፣ ከዚያም በኋላ ባብ «የአዲሱ ዘመን ነቢይ» በመጨረሻም «የአምላኩ ክስተት» መሆኑን በአዋጆች ገለጸ። ከዚህስ በኋላ የፋርስ ባለሥልጣናት ከ[[ቁርዓን]] በ[[ሺርክ]] እንደ ወጣ እንደ ረባሽ ወይም ሀረጤቃ ቆጥረውት አሠሩትና በ[[1842]] ዓም ይሙት በቃ ፈረዱበት።
|