ከ«ርቀት» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
Content deleted Content added
No edit summary |
No edit summary |
||
መስመር፡ 1፦
'''ርቀት''' በነጥቦች ወይንም በነገሮች መካከል ያለ
== ርዝመታዊ ርቀት እና አቀማመጣዊ ርቀት ==
የርቀት
ሰለሞን ጠዋት ከቤቱ ተነስቶ 3 ኪሎ ሜትር ወደ ሥራ ቦታው ቢጓዝ እና ከሰዓት በኋላ ወደ ቤቱ ቢመለስ ፣ የተጓዘው ርቀት ስንት ነው?
አንዱ መልስ፣ ሦስት ወደ ፊት፣ ሦስት ወደ ኋላ፤ በአጠቃላይ ስድስት ኪሎ ሜትር ነው። ይህ ዓይነት የርቀት ትርጓሜ «ርዝመታዊ ርቀት»
ሌላኛው ትርጓሜ፣ «አቀማመጥዊ ርቀት» ሲባል፣ የሰለሞንን አቀማመጥ በመመርመር መልስ ይሰጣል። ሰለሞን ጠዋት በነበረበት ነጥብ ተመልሶ ስለተገኘ፣ የተጓዘው ርቀት [[ዜሮ]] ነው። ማለት አቀማመጡ አልተለወጠም።
==አቀማመጣዊ ርቀት ==
«አቀማመጣዊ ርቀት» በሁለት ነጥቦች መካከል ያለውን ክፍተት በ[[ቀጥታ መስመር]] ይለካል። ለዚህ ምክንያቱ፣ በሁለት ነጥቦች መካከል ያለው ክፍተት በተፈለገ መንገድ ከተለካ፣ ርቀቱ አስተማማኝ መሆኑ ያቆማል። ለምሳሌ፣ ከአዲስ አበባ እስከ ካርቱም 991 ኪሎ ሜትር ነው ቢባል፣ ይህ እርቀት በኬኒያ ተደርጎ ይለካ፣ ወይንም በግብጽ ወይንም በቀጥታ ለይቶ ለማዎቅ ስለማይቻል ዋጋ የለሽ ይሆናል ማለት ነው።
=== የቀጥተኛ ርቀት ምሳሌ ===
[[ስዕል:Egiptian triangle.svg|thumb|
ከጎን ባለው ስዕል
ይሄ ጥያቄ ሊያምታታ ይችላል፣ በተለይ የርቀት ትርጉም ጥርት ባለ መልኩ ካልተሰጠና እንደተፈለገ ከተተርጎም ብዙ አይነት መልስ ሊገኝ ይችላል። ለምሳሌ 3+4 =7 ኪሎ ሜትር ሊባል ይችላል። ይሁንና፣ በሳይንስ ዘንድ የሚሰራበት ትርጓሜ ፣ ከላይ እንደተገለጸው፣ «አቀማመጣዊ ርቀት» ነው። የሚለካውም ከቤቱ እስከ ኳስ ሜዳው የተዘረጋውን ቀጥተኛ መስመር በመያዝ ነው። ከስዕሉ መቁጠር እንደሚቻል፣ ርቀቱ 5ኪሎ ሜትር ሆኖ ይገኛል።
[[አለባብሰው ቢያርሱ ባረም ይመለሱ]] እንዲባል፣ የቃላት ትርጉም ጥርት ብሎ ባልተተርጎመበት ሁኔታ «አስተማማኝ ዕውቀትን» ለመመስረት አይቻልም።፡ ስለሆነም [[የተፈጥሮ ህግጋጋት ጥናት]] ፣ የነጥቦችን አቀማመጥ በትክክል ለይቶ ለመረዳት እንዲቻል፣ ርቀትን በ[[ቀጥታ መስመር]] ይተረጉማል። ይሁንና ይህም የራሱ ችግር አለበት ምክንያቱም አበበ ከሰለሞን 5 ሜትር ርቆ ይገኛል ቢባል፣ በአምስት ሜትር ርቀት ከኋላው ይሁን፣ ከግራው ይሁን፣ ከፊቱ፣ ወዘተ.... ስለማይለይ የራሱ ድክመት አለው። ሥለሆነም የአንድን ነጥብ አንጻራዊ አቀማመጥ በትክክል ለመውቀክ፣ ርቀት እና አቅጣጫ ያስፈልጋሉ። ርቀት እና አቅጣጫ ያለው አንድ መጠን ፣ [[ምዕራፍ]] ይሰኛል፤ ለሳይንስ ጥናት ከፍተኛ ፋይዳ ያለው ጽንሰ ሐሳብ ነው።
==ርቀት እንደ መለኪያ==
በሁለት ነጥቦች ወይም ቦታዎች መካከል ያለ ቀጥተኛ መንገድ ክፍተት በብዙ መንገድ ሊለካ ይችላል። ለምሳሌ የገጠር ሰዎች እንደሚለኩ፣ የሁለት ስፍራዎች ክፍተት በ[[ጊዜ]] ሊለካ ይችላል። ምንም እንኳ እንደዚህ አይነት አለካክ የ[[ብርሃን ፍጥነት]]ን በመጠቀም በከፍተኛ ጥናቶች ቢካሄድም፣ ባብዛኛው ሳይንስ ግን ጥቅም ላይ አይውልም። በምሳሌ ለማየት፣ «ከደሴ እስከ ወልደያ ሁለት ቀን ነው» ሊባል ይችላል። ይሁንና ርቀትን በጊዜ መለካት አስተማማኝ አይሆንም፣ ምክንያቱም አንድ ሰው
በሂደት ሰዎች አስተማማኝ ሆነው ያገኙት መለኪያ [[
==ማጠቃለያ==
ርቀት በሁለት ነጥቦች ያለን ክፍተት በቀጥታ መስመር ይለካል። አለካኩም ይህን ክፍተት ካንድ ቋሚ ክፍተት ጋር በማዎዳደር ነው።
|