ከ«አብርሀም ሊንከን» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
No edit summary
መስመር፡ 5፦
በ[[1838|፲፰፻፴፰]] ዓ.ም. የአሜሪካ ፕሬዚዳንት [[ጄምስ ፖልክ]] በ[[ሜክሲኮ]] ላይ ጦርነት ባደረገ ጊዜ አብርሀም ሊንከን የዚህን ጦርነት ተቃዋሚ ነበሩ። በ[[1846|፲፰፻፵፮]] ዓ.ም. የባርነት ተቃዋሚዎች ወገን [[ሪፐብሊካን ፓርቲ (አሜሪካ)|ሪፐብሊካን ፓርቲ]] መሥርተው አብርሀም ከፍተኛ ሚና አጫወቱ። በ[[1852|፲፰፻፶፪]] ዓ.ም. የፕሬዚዳንትነት ምርጫ ዘመቻ፣ እሳቸው የሪፐብሊካን ዕጩ ሆኑ። ምርጫው በተደረገበት ቀን በ[[ጥቅምት ፳፰]] ቀን [[1853|፲፰፻፶፫]] ዓ.ም.፣ ሊንከን አሸነፉ።
 
ይህም የሆነ የሕዝቡ ብዛት በአገሩ ስሜን እየኖረ የሬፑብሊካን ደጋፊዎች ነበሩ። በስሜኑ ክፍላገሮች ደግሞ፣ ባርነት ከዚህ በፊት ተክለክሎ ነበር። በአሜሪካ ደቡብ በተገኙ ክፍላገሮች ግን ባርነት ገና የተለመደ ከመሆኑ በላይ በ[[ጥጥ]] የተመሠረተው የምጣኔ ሀብታቸው አስፈላጊነት መሰላቸው። ስለዚህ የባርነት ተቃዋሚ ሊንከን ፕሬዚዳንት መሆኑ በደቡብ ያሉት ክፍላገሮች ከአሜሪካ መገንጠላቸው ማለት ነበር። እንዲሁም ከምርጫው ቶሎ ተቀጥሎ ማዕረጉንም እንኳን ገና ሳይይዙ፣ [[ሳውዝ ካሮላይና]] በ[[ታኅሣሥ ፲፪]] ቀን [[1853|፲፰፻፶፫]] ዓ.ም. መገንጠሏን አወጀች። በጥቂት ግዜጊዜ ውስጥ ሌሎች የደቡብ ክፍላገሮች እንዲህ አዋጁና በ[[ጥር ፳፭]] ቀን [[ቴክሳስ]] ፯ኛው ሆነ። ከዚያ ቀጥሎ እነዚህ ፯ ክፍላገሮች በ[[ሞንትጎመሪ፣ አላባማ]] ተባብረው አዲሱ መንግሥት [[የአሜሪካ ኮንፌዴራት ክፍላገሮች]] (CSA) ተባሉ። በ[[የካቲት ፳፮]] ቀን ሊንከን የፕሬዚዳንትነቱን ማዕረግ በተቀበሉበት ቀን አገሩ በተግባር በሁለት ተከፋፍሎ ነበር። የደቡብ ፕሬዚዳንት [[ጄፈርሰን ዴቪስ]] ሆኑ። የደቡብ ክፍላገሮች ለጦርነት ተዘጋጁና ምሽጎች ከUSA ሠራዊት ሊይዙ ጀመር። በ[[ሚያዝያ ፭]] ቀን [[ፎርት ሰምተር]] ምሽግ በሳውስ ካሮላይና በግፍ ስለ ተያዘ ጦርነቱ ጀመረ። ስለዚህ ሊንከን ከስሜኑ ፸፭ ሺ ሰዎች ለዘመቻ ጠሩ። ከዚህ በኋላ ሌላ አራት ደቡብ ክፍላገሮች ተገንጥለው ለCSA ተጨመሩ። የደቡብ ዋና ከተማ ለ[[ዋሺንግተን ዲሲ]] ቅርብ ወደ ሆነው ወደ [[ሪችሞንድ፣ ቪርጂንያ]] ተዛወረ።
 
በጦርነቱ የስሜን ሠራዊት ከብዛታቸው የተነሣ በአራት ዓመት ውስጥ አሸነፉ። በዚህ ጊዜ ላይ ሊንከን ለአመጸኖቹ ባርዮች ነጻነት አዋጁ። ያላመጹ ዜጎች ባርያዎች ግን በዚያን ግዜጊዜ ነጻ አልወጡም። በ[[1856|፲፰፻፶፮]]ዓ.ም.ምርጫ ሊንከን በቀላል ለሁለተኛ ጊዜ ለፕሬዚዳንትነት ተመረጡ። በ[[ሚያዝያ ፪]] ቀን [[1857|፲፰፻፶፯]] ዓ.ም. የኮንፌደራት ሠራዊት እጁን ሰጠ። ነገር ግን [[ሚያዝያ ፯]] ቀን የመድረክ ትርዒት ሲያዩ በነፍሰ ገዳዩ በ[[ጆን ዊልክስ ቡዝ]] እጅ በጥይት ተመትተው በማግሥቱ ሞቱ። ከዚህም ትንሽ በኋላ ባርነት በሕግ በሙሉ ተክለክሎ የተረፉት ባርያዎች ነጻነት አገኙ።
 
[[መደብ:የአሜሪካ መሪዎች]]