ከ«ባቢሎን» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
Bot: Changing የእስያ ታሪክ to
No edit summary
መስመር፡ 25፦
ከሱመር ጽላቶች እንደምናውቅ፣ የኤሪዱ ግንብ ከተተወ በኋላ፣ የሱመር ዋና ከተማ (ዋና ቤተ መቅደስ የተገኘበት) ወደ [[ኒፑር]] ተዛወረ። ከዚያ ዘመን በኋላ የ[[አካድ]] ንጉሥ [[ታላቁ ሳርጎን]] (2070 ዓክልበ. ግድም) አዲስ የዋና መቅደስ ከተማ ወደ ስሜኑ ሠርቶ ማዕረጉን ከኒፑር አንዳዛወረ እናንብባለን። በአንዱ ዜና መዋዕል ዘንድ ሳርጎን «የባቢሎን ጒድጓድ አፈር ቆፍሮ አዲስ ባቢሎን በአካድ ፊት ሠራ»፣ በሌላም «ከጒድጓዱ አፈር ቆፍሮ በአካድ ፊት ከተማ ሠራ፣ ስሙንም 'ባቢሎን' አለው።» ከዚህ መረጃ ሳርጎን የኤሪዱን አፈር ወስዶ አዲሱን ባቢሎን በሥፍራው እንደመሠረተው መገመት እንችላለን። ሳርጎንም እንደ ፊተኛው ኤንመርካር «የአራት ሩቦች ንጉሥ» በመባሉ በሌሎች መንግሥታት ሁሉ በላይ ሆኖ በመላው ዓለም ላይ ይግባኝ ማለት እንደ መጣሉ ነበር።
 
ሆኖም ይህ የኒፑር ቅድምትነት መተካቱ ለጊዜው በሱመራውያን መካከል ተቃውሞ ያገኝ ነበር። ከአካዳውያን፣ [[ጉታውያን]]ና ሱመራውያን ገዥነት በኋላ፣ [[አሞራውያን]] የተባሉት ብሔር ወርሮ አያሌ ከተማ-ግዛቶች መሠረቱ። ከዚህም መካከል አንዱ [[ካዛሉ]] ሲሆን አሞራዊው አለቃ [[ሱሙ-አቡም]] በ1807 ዓክልበ. ግድም የባቢሎን ነጻነት ከካዛሉ አዋጀ፤ በዚያን ጊዜ እሱ የባቢሎን መጀመርያ ንጉሥ ሆነ። ከባቢሎን ነገሥታት [[ሃሙራቢ]] [[የሃሙራቢ ሕግ ፍትሕ]] ስለ መፍጠሩ በተለይ ይታወቃል። የባቢሎን መጀመርያ ውድቅት በ1507 ዓክልበ. ([[ኡልትራ አጭር አቆጣጠር]]) በ[[ኬጥያውያን]] ንጉሥ [[፩ ሙርሲሊ]] እጅ ደረሰ። ከዚያ የኬጥያውያን ጓደኞች የነበሩት [[ካሣውያን]] ብሔር ባቢሎንን ገዛ፣ የከተማውም ስም በ[[ካሣኛ]] «'''ካራንዱኒያሽ'''» ተባለ። እነዚህ ካሣውያን እስከ 1163 ዓክልበ. ድረስ ባቢሎኒያን ገዙ።
 
ለረጅም ዘመናት [[አሦር]] በስሜንና የ[[ባቢሎኒያ]] መንግሥት በደቡብ ለመስጴጦምያ ዋና ተወዳዳሪዎቹ ሆኑ። ከ919 ዓክልበ ጀምሮ አሦር ይበረታ ነበር፤ [[እስራኤል]]ንና [[ግብጽ]]ን እስከሚያሸንፋቸው ድረስ። ከ634 ዓክልበ. በኋላ ግን አሦር ወድቆ ባቢሎኒያ በ[[ናቦፖላሣር]] ሥር እንደገና ነጻነት አገኘ። ልጁም [[ናቡከደነጾር]] ከብሉይ ኪዳን እንደሚታወቅ፣ [[ኢየሩሳሌም]]ን የ[[ይሁዳ]]ንም ሕዝብ የማረከው ([[የባቢሎን ምርኮ]]) ነቢዩም [[ዳንኤል]] የነበየለት ንጉሥ ነው፤ ዳንኤልም [[የናቡከደነጾር የምስል ሕልም]] አስተረጎመለት። ይህ የባቢሎኒያ መንግሥት በ547 ዓክልበ. ለ[[ፋርስ]] ንጉሥ [[ታላቁ ቂሮስ]] ወደቀ።