ከ«የጄኖቫ ቅዱስ መልክ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
ሎሌ፦ መያያዣዎች ወደ 21 ልሳናት አሁን በWikidata ገጽ d:q223246 ስላሉ ተዛውረዋል።
No edit summary
መስመር፡ 2፦
'''የጄኖቫ ቅዱስ መልክ''' በ[[ጄኖቫ]]፣ [[ጣልያን]] በተገኘው [[ቅዱስ በርተሎሜዎስ ቤተ ክርስቲያን]] ውስጥ የሚገኝ [[ስዕል]] ነው። ይህ ስዕል የ[[ኢየሱስ ክርስቶስ]] መልክ ለመግለጽ እንደታሠበ ይታመናል።
 
በአንድ ትውፊት ዘንድ፣ ኢየሱስ በሕይወቱ ስብከት ሳለ የ[[ኤደሣኦስሮኤኔ]] (በ[[ሶርያ]]) ንጉሥ [[5 አብጋር]] በበሽታ ታምመው ኢየሱስ መጥቶ እንዲፈውሳቸው አንድን መልእክተኛ (ሐናን) ወደ [[ኢየሩሳሌም]] ልከው ነበር። ኢየሱስ ወደ ከተማው ወደ [[ኤደሣ]] ለመሔድ ግዜ ስላልነበረው፣ ባንድ ጨርቅ ላይ መልኩን በተአምር አሳተመና ሐናን ስዕሉን ይዞ ወደ ንጉሡ እንዲሔድ ላከው። እንዲህም ሆኖ አብጋር ይህን ስዕል አይተው ከበሽታቸው ተፈወሱና ወዲያው ምዕመን ሆኑ። ስዕሉ ደግሞ በተአምር በመፈጠሩ 'ያለ እጅ የተሠራው' ተብሏል።
 
በጥንታዊ ታሪክ መጻሕፍት መሠረት ይህ ታምራዊ መልክ ያለበት ስዕል እስከ [[936]] ዓ.ም. በኤደሣ ቆይቶ በዚያ አመት ወደ [[ቢዛንታይን]] ዋና ከተማ ወደ [[ቊስጥንጥንያ]] ተዛወረ። እዚህም ፈረንጆች ([[መስቀለኞች]]) ከተማውን እስከ ዘረፉት አመት እስከ [[1196]] ድረስ እንዳደረ ይባላል። ከዚያ በኋላ ምን እንደሆነበት ባይታወቀም ብዙ ቅጂዎች ስለተደረጉበት በ[[አውሮጳ]] አብያተ ክርስቲያናት ውስጥ አንዳንድ ቅጂ ዕውነተኛው መልኩ እንዳሉ የሚል ልማድ አለ። [[Image:39bMandylion.jpg|100px|thumb|በቫቲካን ከተማ ያለው ቅጂ]] እንግዲህ በጄኖቫ ብቻ ሳይሆን በ[[ቫቲካን ከተማ]] [[ሮማ]] ተመሳሳይ ስዕል ቢገኝ እሱ እውነተኛው መሆኑ የሚያምኑ አሉ።