ከ«አንድምታ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
No edit summary
መስመር፡ 1፦
'''አንድምታ''' የሚለው ቃል «'''አንድም'''» ከሚለው የአማርኛ ቃል የመጣ ሲሆን የአረፍተ ነገሮችን ድብቅ ትርጉም አውጥቶ ለማሳየት የሚረዳ መሳሪያ ነው። '''አንድምታ''' ({{en}}exegesis) በ[[ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን]] ውስጥ የመጽሃፍ ቅዱስን ትርጉም ለማወቅ የሚጠቅም የትርጓሜ ሂደት ነው።በአንድምታ መጻህፍቶች ውስጥ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶት ከሁሉ በላይ ትርጓሜ ያገኘው [[የዮሐንስ ራዕይ]] 6፡2 ሲሆን በዚህ ምንባብ የሚገኘው ነጭ ፈረስ 19 አንድምታወች ይዞ ይገኛል<ref>Abraha, Tedros & Kirsten Stoffregen, Encyclopaedia Aethiopica, (edited by Siegbert Uhlig), Harrasowiz Verlag, 2003 </ref>።
 
«አንድ ትርጌሜትርጓሜ እንዲህ ነው፤ '''''አንድም''''' እንዲህ፤ '''''አንድም'''''...» ከማለት እያንዳንዱ ትርጓሜ «አንድምታ» የተባለው ነው፣ «አንድምታ» ለመላው ትምህርት ዘርፍ ለመሰይም ችሏል።
 
የአንድምታ መጻህፍት የመጽሃፍ ቅዱሳትን እንግዳ ቦታወችና አስተሳሰቦች ከ18ኛው ክፍለዘመን ኢትዮጵያ ቦታወችና አስተሳሰቦች አንጻር በማገናዘብ ያስረዳሉ። ለአንድምታ መነሳትና መስፋፋት ከፍተኛ ሚና የነበረው የፖርቱጋል ካቶሊኮች በአጼ [[ፋሲለደስ]] መባረር ነበር። ከዚህ በኋላ በተካሄደው ስራ [[መምህር ኢሶዶሮስ]] እና ከሱ በኋላ የተነሳው [[አቃቤ ሰዓት ሃብቴ]] በሰፊው ለዚህ ስራ በማበርከት ይጠቀሳሉ። ስለዚህ ሰፊ ጥረታቸው የአንድምታ ትምህርት ከቅኔና ከንባብ ቤት ትምህርት ማለፍ ቀጥሎ የሚሰጥ ልዩ ትምህርት ሆነ።