ከ«አንድምታ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
Content deleted Content added
No edit summary |
ጥNo edit summary |
||
መስመር፡ 1፦
'''አንድምታ''' የሚለው ቃል «'''አንድም'''» ከሚለው የአማርኛ ቃል የመጣ ሲሆን የአረፍተ ነገሮችን ድብቅ ትርጉም አውጥቶ ለማሳየት የሚረዳ መሳሪያ ነው። '''አንድምታ''' ({{en}}exegesis) በ[[ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን]] ውስጥ የመጽሃፍ ቅዱስን ትርጉም ለማወቅ የሚጠቅም የትርጓሜ ሂደት ነው።በአንድምታ መጻህፍቶች ውስጥ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶት ከሁሉ በላይ ትርጓሜ ያገኘው [[የዮሐንስ ራዕይ]] 6፡2 ሲሆን በዚህ ምንባብ የሚገኘው ነጭ ፈረስ 19 አንድምታወች ይዞ ይገኛል<ref>Abraha, Tedros & Kirsten Stoffregen, Encyclopaedia Aethiopica, (edited by Siegbert Uhlig), Harrasowiz Verlag, 2003 </ref>።
«አንድ
የአንድምታ መጻህፍት የመጽሃፍ ቅዱሳትን እንግዳ ቦታወችና አስተሳሰቦች ከ18ኛው ክፍለዘመን ኢትዮጵያ ቦታወችና አስተሳሰቦች አንጻር በማገናዘብ ያስረዳሉ። ለአንድምታ መነሳትና መስፋፋት ከፍተኛ ሚና የነበረው የፖርቱጋል ካቶሊኮች በአጼ [[ፋሲለደስ]] መባረር ነበር። ከዚህ በኋላ በተካሄደው ስራ [[መምህር ኢሶዶሮስ]] እና ከሱ በኋላ የተነሳው [[አቃቤ ሰዓት ሃብቴ]] በሰፊው ለዚህ ስራ በማበርከት ይጠቀሳሉ። ስለዚህ ሰፊ ጥረታቸው የአንድምታ ትምህርት ከቅኔና ከንባብ ቤት ትምህርት ማለፍ ቀጥሎ የሚሰጥ ልዩ ትምህርት ሆነ።
|