ከ«ጌባል» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
ሎሌ፦ መያያዣዎች ወደ 45 ልሳናት አሁን በWikidata ገጽ d:q173532 ስላሉ ተዛውረዋል።
No edit summary
መስመር፡ 3፦
የጥንቱ [[ፊንቄ]] ታሪክ ጸሐፊ [[ሳንኩኒያቶን]] እንዳለ፣ ጌባል ከሁሉ ጥንታዊ ከተማ ሲሆን በንጉሡ [[ክሮኖስ]] (ወይም 'ኤሎስ') በፊንቄ ([[ከነዓን (ጥንታዊ አገር)|ከነዓን]]) አገር ተመሠርቶ ነበር። ለረጅም ጊዜ ከተማው የ[[ምስር]] [[ፈርዖን]] ጓደኛ ነበር። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በ[[መዝሙረ ዳዊት]] 83፡7 እና [[ትንቢተ ሕዝቅኤል]] 27፡9 ይጠቀሳል። በኋላ (747 ዓክልበ.) ጌባል ለ[[አሦር]] ንጉሥ [[3 ቴልጌልቴልፌልሶር]] ተገዥ ሆነ። እንዲሁም በየተራው ወደ [[ፋርስ]]፣ [[መቄዶን]] እና [[ሮማ]] መንግሥታት ተዛወረ፤ ከዚያም ለአረቦች ወደቀ። በ[[መጀመርያው መስቀል ጦርነት]] ([[1092]] ዓ.ም) ስሙ 'ጊብለት' ተብሎ ለጊዜ የፈረንጆች ማዕከል ሆነ። ከ[[1508]] እስከ [[1911]] ዓ.ም. በ[[ኦቶማን]] (ቱርክ) መንግሥት ነበር። ከተማው እስከ ዛሬ ድረስ በሊባኖስ ይገኛል።
 
በጥንት ጌባል [[ፓፒሩስ]] ([[ቄጠማ]] ወይም የ[[ወረቀት]] ተክል) ወደ ግሪኮች የነገደው ዋናው ወደብ ስለ ሆነ፣ ግሪኮችም የከተማውን ስም Βύβλος /ቢውብሎስ/ ስላሉት፤ ይህ ስም በግሪክ ቋንቋ ደግሞ 'ፓፒሩስ' ወይም 'መጽሐፍ' ማለት ሆነ። ይህም ቃል በ[[እንግሊዝኛ]] (በ[[ታላቅ የአናባቢ መፈራረቅ]] ምክንያት) የ«Bible» (/ባይብል/፣ [[መጽሐፍ ቅዱስ]]) ምንጭ ሆነ።
 
[[መደብ:የቀድሞ ከተሞች]]