ከ«የዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ድምፅ መልዕክት ወደ ንግሥት ቪክቶሪያ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
ጽሑፉ በ«==ማጣቀሻ == <references/> መደብ:አጼ ምኒልክ» ተተካ።
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ
መስመር፡ 1፦
[[File:የዳግማዊ ዓፄ ምንሊክ ድምጽ መልዕክት ወደ ቪክቶሪያ.ogg|right|thumb|የዓፄ ምኒልክ የድምጽ መልዕክት]]
'''የዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ድምፅ መልዕክት ወደ ንግሥት ቪክቶሪያ''' በ[[1891|፲፰፻፺፩]] ዓ.ም. [[ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ]] ለእንግሊዟ [[ንግሥት ቪክቶሪያ]] በ[[ፎኖግራፍ]] ድምፅ መቅርጫ አድርገው የላኩት የድምፅ ደብዳቤ ነበር<ref>http://paperspast.natlib.govt.nz/cgi-bin/paperspast?a=d&d=HBH18990331.2.38</ref>። ይህንን መልክት በ[[አዲስ አበባ]] የ[[ብሪታኒያ]]ው ዋና መላክተኛ ጆን ሌን ሃሪንግቶን [[ግንቦት ፳፯]] ቀን [[1891|፲፰፻፺፩]] ዓ/ም ለብሪታኒያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በላከው ደብዳቤ መረከቡን ሲገልጽ በቅጅው ላይ የ[[እቴጌ ጣይቱ]]ም ድምጽ አብሮ መቀረጹን ይገልጻል።
 
የጃንሆይ ምኒልክ ደብዳቤ በሰላምታና በመልካም ምኞት ላይ ሲያተኩር፣ እንዲሁም በቅርቡ የተካሄደውን የ[[ዩናይትድ ኪንግደም|እንግሊዝ]]ን በ[[ሱዳን]] ላይ ድል በማስመልከት የ[[መተማ]] ከተማ የኢትዮጵያ እንደሆነ ንግሥቲቱ እንዲወስኑ ያሳውቃል። ከጎን ፋይሉ ቀርቧል። ከዚህ በታች ደግሞ መልዕክቱ ቃል በቃል ምን እንደሚል በጽሑፍ ቀርቧል።
 
<blockquote>«እኔ ዳግማዊ ምኒልክ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ እጅግ ለከበሩ ወዳጃችን ቪክቶሪያ የታላቅ የእንግሊዝ ሕዝብ የሕዝብ ነገሥታት መድኃኔ ዓለም ጤና ይስጥልኝ እላለሁ።<br/><br/>
 
በሙሴ ሃሪንግቶን እጅ እጅግ የተዋበ ያማረ የንግሥት ፎኖግራፍ ሲደርስልኝ የከበሩ ንግሥት ድምፅ አጠገቤ ሆነው ስሰማ በብዙ ደስታ አደመጥኩ።<br/><br/>
 
ለኛና ለመንግሥቴ ስለ መልካም ምኞትዎ እግዚአብሔር ያመስግንዎ። ለርስዎ ዕድሜና ጤና ለሕዝብዎ ሰላምና ዕረፍት እግዚአብሔር ይስጥዎ። በሁለታችን ሕዝብ መካከል ያለውን ጉዳይ ሁሉ ከሙሴ ሃሪንግቶን ጋር ተነጋገርኩ። እርሱም አሁን ወደ እንግሊዝ አገር እመለሳለሁ ቢለኝ ጉዳያችንን ሁሉ አቃንተህ ብትመለስ ደስ ይለኛል ብዬ ነገርኩት። አሁን ደግሞ ንግሥት በደህና እንዲቀበሉት።<br/><br/>
 
ደግሞ የመተማ ነገር የእኛ ታላቁ ንጉሣችንና ብዙ የአገራችን ሰዎች ስለኃይማኖታቸው እልህ ብለው የሞቱበትን ለሙሴ ሃሪንግቶን ነግረነዋልና ይህንን ከተማ የእንግሊዝ መንግሥት እንዲያውቅልን እርስዎ ይረዱናል ብዬ ተስፋ አለኝ።<br/><br/>
 
ኢትዮጵያ እና የእንግሊዝ አገር በሰላምና በፍቅር እንዲኖሩ እግዚአብሔር ይርዳን ብዬ ለታላቅ ሕዝብዎ የክብር ሰላምታዬን አቀርባለሁ።»</blockquote>
 
==ማጣቀሻ ==
<references/>