ከ«ክርስትና» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
No edit summary
መስመር፡ 3፦
የክርስትና መጀመርያ የሚተረክበት [[አዲስ ኪዳን]] በተለይም [[ወንጌል]]ና [[የሐዋርያት ሥራ]] ነው። [[የቅሌምንጦስ ስነ ጽሑፍ]] እንደሚለው ረቢ ኢየሱስ በ[[ይሁዳ]] ክፍላገር ገና ሲያስተምር፣ ደቀ መዝሙሩ [[ባርናባስ]] በ[[ሮሜ]] ከተማ አደባባይ ቆሞ ኢየሱስ [[መሲኅ]] መሆኑን አዋጀ፤ ይህ ታሪክ ግን አሁን በምዕራባውያን መምኅሮች ዘንድ አጠያያቂ ሆኗልና በሰፊ አይታወቅም። በሌላ ልማድ ኢየሱስ ለ[[ኦስሮኤና]] ንጉሥ ለ[[5ኛው አብጋር]] ደብዳቤ ጻፈ፣ ታዓምራዊ መልክም እንደ ላካቸው ይባላል ([[የጄኖቫ ቅዱስ መልክ]] ይዩ።)
 
በወንጌል መሠረት ኢየሱስ ከተሰቀለ በኋላ፣ እንደገና በሕይወት ከመቃብር ተነሥቶ ለደቂቀ መዝሙሮቹ እንደገና ታይቶ ከዚያ ወደ ሰማይ ዓረገ። ከዚህ በኋላ የ[[አይሁድ]] ጉባኤ [[ቅዱስ ጴጥሮስ|ጴጥሮስ]]ንና ሌሎችን ሐዋርያት አስገረፋቸው፣ በኢየሱስ ስም እንዳያስተምሩ ከለከሉዋቸው። ጴጥሮስ ግን፦ «ከሰው ይልቅ ለ[[እግዚአብሔር]] ልንታዘዝ ይገባል» ብሎ መለሳቸው (የሐዋርያት ሥራ 5:29)።
 
[[የኢየሱስ ወንድም ያዕቆብ]] በ[[ኢየሩሳሌም]] የቤተክርስቲያን መጀመርያ መሪ ሆኑ። ከትንሽ በኋላ አይሁድ ያልሆኑ አሕዛብ ምዕመናን እንዲሆኑ ፈቀደ፣ [[ግርዘት]] ወይም ሌሎች የ[[ሕገ ሙሴ]] ከባድ ደንቦች አላስገደዳቸውም፣ ነገር ግን ከሕገ ሙሴ «ለጣዖት ከተሠዋ፣ ከደምም፣ ከተናቀም (ከመብላት)፣ ከዝሙትም ትርቁ ዘንድ» አስገደዳቸው (የሐዋርያት ሥራ 15)። ከዚያ በተለይ በ[[ቅዱስ ጳውሎስ]] ስብከት ምክንያት ክርስትና ወንጌልም በቶሎ በ[[ሮማ መንግሥት]] እስከ ሮሜ ከተማ ድረስ ተስፋፋ። በተጨማሪ ልዩ ልዩ ሐዋርያት ወንጌሉን እስከ [[አክሱም መንግሥት]]ና እስከ [[ሕንድ]] ድረስ ቶሎ ወሰዱ።