ከ«ክርስትና» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
Content deleted Content added
No edit summary |
|||
መስመር፡ 5፦
በወንጌል መሠረት ኢየሱስ ከተሰቀለ በኋላ፣ እንደገና በሕይወት ከመቃብር ተነሥቶ ለደቂቀ መዝሙሮቹ እንደገና ታይቶ ከዚያ ወደ ሰማይ ዓረገ። ከዚህ በኋላ የ[[አይሁድ]] ጉባኤ [[ጴጥሮስ]]ንና ሌሎችን ሐዋርያት አስገረፋቸው፣ በኢየሱስ ስም እንዳያስተምሩ ከለከሉዋቸው። ጴጥሮስ ግን፦ «ከሰው ይልቅ ለ[[እግዚአብሔር]] ልንታዘዝ ይገባል» ብሎ መለሳቸው (የሐዋርያት ሥራ 5:29)።
[[የኢየሱስ ወንድም ያዕቆብ]] በ[[ኢየሩሳሌም]] የቤተክርስቲያን መጀመርያ መሪ ሆኑ። ከትንሽ በኋላ አይሁድ ያልሆኑ አሕዛብ ምዕመናን እንዲሆኑ ፈቀደ፣ [[ግርዘት]] ወይም ሌሎች የ[[ሕገ ሙሴ]] ከባድ ደንቦች አላስገደዳቸውም፣ ነገር ግን ከሕገ ሙሴ «ለጣዖት ከተሠዋ፣ ከደምም፣ ከተናቀም (ከመብላት)፣ ከዝሙትም ትርቁ ዘንድ»
በ41 ዓም የሮሜ ቄሣር [[ክላውዴዎስ]] «አይሁዶችን» ከሮሜ ከተማ ባስወጣቸው ዘመን፣ ብዙዎቹ ክርስቲያኖች እንደ ነበሩ ይመስላል። ክርስቲያኖች በሮሜ መንግሥት ብዙ ጊዜ እስከ [[303]] አም ድረስ ከቄሣሮቹ መከራዎች ቢያገኙም፣ ሃይማኖቱ ግን ምንጊዜም እየተበዛ ነበር።
|