ከ«ባቢሎን» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
Content deleted Content added
አስፋፋ |
No edit summary |
||
መስመር፡ 23፦
መጀመርያው «ባቢሎን» የደቡብ [[ሱመር]] ከተማ የ[[ኤሪዱ]] መጠሪያ ስም እንደ ነበር ይመስላል። በ[[ሱመራውያን ነገሥታት ዝርዝር]] ዘንድ፣ ክ[[ማየ አይኅ]] ቀጥሎ ኤሪዱ የዓለሙ መጀመርያው ከተማ ሲሆን፣ ንጉሡ [[ኤንመርካር]] (2450 ዓክልበ. አካባቢ) ታላላቅ [[ዚጉራቶች]]ን (የቤተ መቅደስ ግንቦች) በኤሪዱ እና በ[[ኦሬክ]] እንዳሠራ ይለናል። ይህም በሌሎች ልማዶች እንደሚተረክ የባቢሎንና የኦሬክ መሥራች [[ናምሩድ]] ግንቡን በባቢሎን እንደ መሥራቱ ታሪክ ይመስላል።
ከሱመር ጽላቶች እንደምናውቅ፣ የኤሪዱ ግንብ ከተተወ በኋላ፣ የሱመር ዋና ከተማ (ዋና ቤተ መቅደስ የተገኘበት) ወደ [[ኒፑር]] ተዛወረ። ከዚያ ዘመን በኋላ የ[[አካድ]] ንጉሥ [[ታላቁ ሳርጎን]] (2070 ዓክልበ. ግድም) አዲስ የዋና መቅደስ ከተማ ወደ ስሜኑ ሠርቶ ማዕረጉን ከኒፑር አንዳዛወረ እናንባለን። በአንዱ ዜና መዋዕል ዘንድ ሳርጎን «የባቢሎን ጒድጓድ አፈር ቆፍሮ አዲስ ባቢሎን በአካድ ፊት ሠራ»፣ በሌላም «ከጒድጓዱ አፈር ቆፍሮ በአካድ ፊት ከተማ ሠራ፣ ስሙንም 'ባቢሎን' አለው።» ከዚህ መረጃ ሳርጎን የኤሪዱን አፈር ወስዶ አዲሱን ባቢሎን በሥፍራው እንደመሠረተው መገመት
ሆኖም ይህ የኒፑር ቅድምነት መተካቱ ለጊዜው በሱመራውያን መካከል ተቃውሞ ያገኝ ነበር። ከአካዳውያን፣ [[ጉታውያን]]ና ሱመራውያን ገዥነት በኋላ፣ [[አሞራውያን]] የተባሉት ብሔር ወርሮ አያሌ ከተማ-ግዛቶች መሠረቱ። ከዚህም መካከል አንዱ [[ካዛሉ]] ሲሆን አሞራዊው አለቃ [[ሱሙ-አቡም]] በ1807 ዓክልበ. ግድም የባቢሎን ነጻነት ከካዛሉ አዋጀ፤ በዚያን ጊዜ እሱ የባቢሎን መጀመርያ ንጉሥ ሆነ። {{መዋቅር-ታሪክ}}
|