ከ«ኡራርቱ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
No edit summary
መስመር፡ 4፦
ስያሜው «ኡራርቱ» [[አሦርኛ]] ሲሆን ከደብረ አራራት ስም ጋር እንደ ተዛመደ ይታሥባል። በአሦርኛ ሰነዶች «ኡራርቱ»ና «[[ናይሪ]]» የሚሉት ስሞች ለዙሪያው ከ1300 ዓክልበ. አካባቢ ጀምሮ ተዘግበዋል። በተጨማሪ በ[[ሱመር]] አፈ ታሪክ «[[አራታ]]» የተባለ ሀገር ምናልባት 2450-2350 ዓክልበ. ይታወቅ ነበር፣ እሱም ከአሶርኛው «ኡራርቱ» ጋር ዝምድና እንዳለው የሚያስቡ አሉ። በ[[ትንቢተ ኤርምያስ]] ([[ብሉይ ኪዳን]] 600 ዓክልበ. አካባቢ) ደግሞ በ51:27 የአራራት፣ የ[[ሚኒ]] እና የ[[አስከናዝ]] መንግሥታት ሲጠቅስ፣ ይህ «አራራት መንግሥት» ማለት በዚያን ጊዜ የነበረው የኡራርቱን መንግሥት ይገልጻል። በ[[ኡራርትኛ]] የመንግሥቱ ስም «'''ቢያይኒሊ'''» ተባለ።
 
ከአሦርኛ መዝገቦች እንደምናውቅ፣ ከ1300 እስከ 852 ዓክልበ. ድረስ እነዚህ «ናይሪ» ወይም «ኡራይትሪኡሯትሪ» ብሔሮች በተለያዩ ነገዶች ይኖሩ ነበር፤ በ852 ዓክልበ. የናይሪ ሕዝቦች በንጉሥ [[አራሙ]] ተባብረው የኡራርቱ (ቢያይኒሊ) መንግሥት ፈጠሩ።
[[ስዕል:Spitzhelm urartaisch.JPG|300px|thumb|left|የኡራርቱ የራስ ቁር]]
በቋንቋ ረገድ ኡራርትኛ ከበፊቱ [[ሑርኛ]] ጋር ተዛመደ። [[ሑራውያን]] በተለይ ከ2075-1300 አክልበ በስሜን [[መስጴጦምያ]] ይታወቁ ነበር።