ከ«ጆሰፍ ስሚስ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
አዲስ ገጽ ፈጠረ፦ «300px|thumb|ጆሰፍ ስሚስ 1835 ዓም ፎቶ '''ጆሰፍ ስሚስ''' (1798-1836 ዓም) ...»
 
No edit summary
መስመር፡ 4፦
ጆሰፍ ስሚስ በ[[ክርስቲያን]] ኅብረተሠብ የተወለደው ቢሆንም፣ በወጣትነቱ እንደ [[አስማተኛ]] ዝነኛ ሆኖ ነበር። በ«[[ንግርተኛ ድንጋዮች]]» እርዳታ የጠፉትን ቅርሶች ለማግኘት ችሎታው እንደ ነበረው ማሳመን ቢሞክር፣ በማናቸውም ፈተና ይህ ዘዴ ሐሣዌ መሆን ሲገለጽ፣ ከድፍረቱ ግን አልዞረም ነበር።
 
በ1820 ዓም «[[ሞሮኒ]]» የተባለ አንድ መልአክ «[[የወርቅ ጽላቶች]]ን» እንዳሳዩት ብሎ እነኚህን ጽላቶች ወደ እንግሊዝኛ በ«ንግርተኛ ድንጋዮች» ለማስተርጐም ዋንዋና እቅዱ ሆነ። ስሚስ እንዳለው ጽላቶቹ የተቀረጹበት ቋንቋ «[[ተሐድሶ ግብጽኛ]]» እንደ ነበር አለ። ለመሆኑ በዚህ ዘመን ያሕል የታሪካዊ [[ግብጽኛ]] ማንበብ ችሎታ እየተፈታ ሲሆን፣ ስሚስ በእውነት ስለ ግብጽኛ ወይም ስለ ቋንቋ ጥናት ያወቀው ብዙ ነገር እንዳልነበረ ግልጽ ነው።
[[ስዕል:JosephSmithTranslating.jpg|250px|thumb|left|ጆስፍጆሰፍ ስሚስ ድንጋዮቹን አይቶ የመጽሐፈ ሞርሞን ትርጉም ሲያወራ]]
የወርቅ ጽላቶችጽላቶቹ በሰዎች መቸም አልታዩም፤ ስሚስ እንዳለው እያስተረጎማቸው አንድላይ ከሱ ጋር መኖራቸው አስፈላጊ አልነበረም፣ በመላዕክት እርዳታ ነው ብሎ ድንጋዮቹን በመመልከት የጽሑፉን እንግሊዝኛ ትርጉም በቃል ያወራ ነበር፤ ጓደኞቹም ከዚያ ያወራውን ይጽፉ ነበር። እንዲህ [[መጽሐፈ ሞርሞን]] ተፈጠረ። በዚህ መጽሐፍ ዘንድ አይሁዶች በጥንት ከ[[እስራኤል]] ወጥተው ወደ አሜሪካ ፈለሱ፤ በኋላም [[ኢየሱስ ክርስቶስ]] ደግሞ ወደ እነርሱ በአሜሪካ መጣላቸው ይላል።
 
በስሚስ ኗሪ ክፍላገር በ[[ኒው ዮርክ]] የነበሩት ሕዝብ በአጠቃላይ ስለ ተቃወሙት፣ ከተከታዮቹ ጋር ወደ ምዕራብ ሸሹ። በአዲስ ሃይማኖቱ ከክርስትና ከሚለዩ ትምህርቶች መካከል፣ [[ሥላሴ]]ን አያስተምርም፣ ኢየሱስና እግዚአብሔር የተለያዩ ናቸው፣ ስሚስ ነቢዩ ነው፣ በተጨማሪ «አንድ ባንድ» ሳይሆን አንዱ ሰው አያሌ ሚስቶች ማግባት መልካም እንደ ሆነ ሁሉ የሚያስተምር ሃይማኖት ሆነ።
 
አንድ ጊዜ የእውነተኛ ግብጽኛ ብራና ከነጋዴ ገዝቶ ይህን ደግሞ «አስተረጎመ»። በጆሰፍ ስሚስ ትርጉም ጽሑፉ የሞርሞኖች «[[መጽሐፈ አብርሃም]]» ሆነ። ይህም ብራና አሁን ለሊቃውንት ታውቆ ግን ምንም ስለ [[አብርሃም]] የሚል ነገር ሳይሆን፣ በውኑ የግብጻውያን «[[መጽሐፈ ሙታን]]» ቅጂ መሆኑን ገለጹ። ሆኖም ሞርሞኖች እስካሁን የስሚስ ብልሃትና ቅንነት ደጋፊዎች ናቸው።
 
ስሚስ ደግሞ [[ደብረ ጽዮን]] እና [[አዲስ ኢየሩሳሌም]] በውነት በጣም ለጥ ባለ ቦታ በ[[ሚዙሪ]] ክፍላገር እንደ ተገኙ አስተማረ። በዚህ ስፍራ ግን እጅግ ለጥ ብሎ ምንም ተራራ በፍጹም አይታይም። ያም ሆነ ይህ እስካሁን ድረስ በብዙ ሞርሞኖች እንደ ተቀደሰ ቦታ ይቆጠራል።