ከ«የንቅያ ጸሎተ ሃይማኖት» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
አዲስ ገጽ ፈጠረ፦ «320px|thumb '''የንቅያ ጸሎተ ሃይማኖት''' በአብዛኞቹ አብያተ ክርስቲያናት የሚቀበል የ[...»
(No difference)

እትም በ02:32, 11 ማርች 2017

የንቅያ ጸሎተ ሃይማኖት በአብዛኞቹ አብያተ ክርስቲያናት የሚቀበል የክርስትና እምነት መግለጫ ነው።

እንዲያውም የዛሬው ጸሎት ከንቅያ ጉባኤ በኋላ፣ በቁስጥንጥንያ ጉባኤ የተዘጋጀው ነው። ሁለተኛው ጉባኤ አንዳንድ ቃላት በተለይም ስለ መንፈስ ቅዱስ በይበልጥ የሚገለጽ ቋንቋ ጨመረ። በመጀመርያውም እትም፣ መጨረሻው ዓረፍተ ነገር ሀረ ጤቆች ይወገዙ ይል ነበር፤ በዚህ ፈንታ አዲሱ ጸሎተ ሃይማኖት የጥምቀትየሙታን ትንሳኤና ዘላለም ሕይወት እምነቶች ይጠቅሳል።

ከ372 ዓም ጀምሮ እስካሁን በምንም ሳይቀየር በተዋሕዶምሥራቅ ኦርቶዶክስሮማን ካቶሊክፕሮቴስታንት አብያተ ክርስቲያን ሁሉ በሙሉ ይቀበላል። ሞርሞኖች ወይም የይሆዋ ምሥክሮች ግን ሥላሴን የማይቀበሉ እምነቶች ናቸው።

የሃይማኖት ጸሎት (የተሻለው 372 ዓ.ም. ቁስጥንጥንያ እንደ ተዘጋጀ)

ኹሉን በያዘ፣ ሰማይንና ምድርን፥ የሚታየውንና የማይታየውን በፈጠረ፡ አንድ አምላክ በሚኾን፡ በእግዚአብሔር አብ እናምናለን።

ዓለም ሳይፈጠር፡ ከእርሱ ጋራ በነበረ፥ አንድ የአብ ልጅ፥ አንድ ጌታ በሚኾን፡ በእግዚአብሔር ወልድም እናምናለን። እርሱም፡ ከብርሃን የተገኘ ብርሃን፥ ከእውነተኛ አምላክ የተገኘ አምላክ፥ የተወለደ እንጂ፡ ያልተፈጠረ፣ በመለኮቱ፡ ከአብ ጋራ የሚተካከል፣ ኹሉ፡ በእርሱ የኾነው፡ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። በሰማይ ካለው፣ በምድርም ካለው፡ ያለእርሱ፡ ምንም ምን፡ የኾነ የለም።

ስለእኛ ስለሰዎች፥ እኛን ለማዳን፡ ከሰማይ ወረደ፤ በመንፈስ ቅዱስ ግብር፡ ከቅድስት ድንግል ማርያም፡ ከሥጋዋ፡ ሥጋ፥ ከነፍሷ፡ ነፍስ ነሥቶ፡ ፍጹም ሰውን ኾነ። በጴንጤናዊው ጲላጦስ ዘመን፡ ስለእኛ፡ መከራን ተቀበለ። ተሰቀለ። ሞተ። ተቀበረ። በሦስተኛውም ቀን፡ ከሙታን ተለይቶ ተነሣ። በክብር፥ በምስጋና፡ ወደሰማይ ዐረገ። በአባቱም ቀኝ፡ በዙፋኑ ተቀመጠ። ዳግመኛም፡ በሕያዋንና በሙታን ለመፍረድ፡ በምስጋና ይመለሳል። ለመንግሥቱ፡ ፍጻሜ የለውም።

በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስም እናምናለን። እርሱም፡ ሕይወትን የሚሰጥ፣ ከአብ የሠረፀና በነቢያት ዐድሮ የተናገረው፥ በሓዋርያት ላይ የወረደውና በኢየሱስ ክርስቶስ ቤዛነት፡ ዓለሙን፡ በጸጋው የሞላው፡ ቅዱሱ የእውነት መንፈስ ነው። ለእርሱም፡ ከአብና ከወልድ ጋራ፡ በአንድነት እንሰግድለታለን፤ እናመሰግነዋለንም።

በአንዲት ቅድስት ካቶሊክ እና ሐዋርያዊው ቤተ ክርስቲያን እናምናለን።

ኃጢኣት በሚሠረይባት፡ በአንዲት ጥምቀት እናምናለን።

በሙታን ትንሣኤ፥ በዘለዓለምም ሕይወት እናምናለን። ለዘለዓለሙ፤ አሜን።

በመጀመርያው ንቅያ ጉባኤ በ317 ዓ.ም. እንደ ተጻፈ

ኹሉን በያዘ፣ የሚታየውንና የማይታየውን በፈጠረ፡ አንድ አምላክ በሚኾን፡ በእግዚአብሔር አብ እናምናለን።

ከእርሱ ጋራ በነበረ፥ የአብ ልጅ፥ አንድ ጌታ በሚኾን፡ በእግዚአብሔር ወልድም እናምናለን። እርሱም፡ ከብርሃን የተገኘ ብርሃን፥ ከእውነተኛ አምላክ የተገኘ አምላክ፥ የተወለደ እንጂ፡ ያልተፈጠረ፣ በመለኮቱ፡ ከአብ ጋራ የሚተካከል፣ ኹሉ፡ በእርሱ የኾነው፡ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። በሰማይ ካለው፣ በምድርም ካለው፡ ያለእርሱ፡ ምንም ምን፡ የኾነ የለም።

ስለእኛ ስለሰዎች፥ እኛን ለማዳን፡ ወረደ፤ ነፍስ ነሥቶ፡ ፍጹም ሰውን ኾነ። መከራን ተቀበለ። በሦስተኛውም ቀን፡ ከሙታን ተለይቶ ተነሣ። ወደሰማይ ዐረገ። ዳግመኛም፡ በሕያዋንና በሙታን ለመፍረድ፡ ይመለሳል።

በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስም እናምናለን።

ነገር ግን፣ «ያልተገኘበት ዘመን ነበር» እና «ሳይፈጠር አልነበረም» እና «ከአንዳችም ተፈጠረ»፣ ወይም «ከሌላ ባሕርይ ነው» ወይም «የእግዚአብሔር ይፈጠራል» ወይም «የሚለወጥ ነው» የሚሉት፦ በቅድሥት ካቶሊክ እና ሐዋርያዊው ቤተ ክርስቲያን ዘንድ ይወገዙ።