ከ«አማራ (ክልል)» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
አንድ ለውጥ 335324 ከ197.156.75.54 (ውይይት) ገለበጠ - አይሆንም
አማርኖ
Tag: blanking
መስመር፡ 1፦
አማርኛ0923652276
{{የቦታ መረጃ
| ስም = አማራ ክልል
| ቦታ_ዓይነት = ክልል
| ይፋ_ስም =
| ስዕል = Amhara_in_Ethiopia.svg
| ስዕል_መግለጫ = የአማራ ክልልን በቀይ የሚያሳይ የኢትዮጵያ ካርታ
| ባንዲራ = Flag_of_the_Amhara_Region.svg
| አርማ =
| ክፍፍል_ዓይነት = አገር
| ክፍፍል_ስም = [[ኢትዮጵያ]]
| ክፍፍል_ዓይነት2 =
| ክፍፍል_ስም2 =
| ምሥረታ_ስም =
| ምሥረታ_ቀን =
| ምሥረታ_ስም2 =
| ምሥረታ_ቀን2 =
| መቀመጫ_ዓይነት = ርዕሰ ከተማ
| መቀመጫ = [[ባህር ዳር]]
| መሪ_ማዕረግ =
| መሪ_ስም =
| መሪ_ማዕረግ2 =
| መሪ_ስም2 =
| ቦታ_ጠቅላላ = 194,709<ref name="csa">{{cite web|title=፳፻፬ ዓ.ም. ብሔራዊ ስታቲስቲክስ|url=http://www.csa.gov.et/images/documents/pdf_files/nationalstatisticsabstract/2011/2011%20population.pdf|publisher=ማዕከላዊ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ|accessdate=ሰኔ ፳፪ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም.}}</ref>
| ቦታ_መሬት =
| ቦታ_ውሃ =
| ከፍታ =
|በክልሉ የሚኖረው
| ሕዝብ_ጠቅላላ =35,875,702<ref name="csa" /> (25,987,678 በአማራ ክልል እሚኖር ሲሆን የተቀረው በሌላው የሀገሬቱ ክፍል ይኖራል)
| ሕዝብ_ከተማ =
| ሕዝብ_ገጠር =
| ድረ_ገጽ =
| lat_deg =
| lat_min =
| north_south =
| lon_deg =
| lon_min =
| east_west =
}}
'''አማራ''' (ክልል 3) ከዘጠኙ የ[[ኢትዮጵያ]] ክልሎች አንዱ ሲሆን ከ 1994 በፊት አራት የሀገሪቱን ዋና ወና ክፍለ ሀገራት የ ካትት ነበር እነሱም በጌምድር ጐጃም ወሎና ሸዋ ነበሩ ።የአማራ ብሔራዊ ክልል ጅኦግራፊያዊ አቀማመጥ በ8° 45 እስከ 13° 45 ሰሜን የኬንትሮስ እና በ35° 46 እስከ 40° 25 ምስራቅ የኬንትሮስ መስመር ውስጥ ይገኛል። በምስራቅ የ[[አፋር (ክልል)|አፋር]]ና የ[[ኦሮሚያ ክልል|ኦሮሚያ]] ክልሎች፣ በምዕራብ [[ሱዳን]] እና [[ቤንሻንጉል-ጉምዝ ክልል]]፣ በሰሜን የ[[ትግራይ ክልል]]ና በደቡብ የኦሮሚያ ክልል ያዋስኑታል። የቆዳ ስፋቱ ፻፶፯ሺ፸፮ ካሬ ሜትር ሲሆን ከአገሪቱ አሥራ አምስት በመቶ ድርሻ ይይዛል። የክልሉ ሕዝብ ብዛት ደግሞ በ[[2002|፳፻፪]] ዓ/ም 20,875,456 እንደነበር የተገመተ ሲሆን ከአገሪቱ ጠቅላላ ሕዝብ 33.9% አካባቢ ድርሻ ይይዛል ተብሎ ይገመታል።
ክልሉ በ፲ ዞኖችና በ፻፷፮ የገጠርና የከተማ ወረዳ አስተዳደሮች የተከፋፈለ ሲሆን ከዚህ ውስጥ ፴፰ የሚሆኑት የከተማ አስተዳደሮች ናቸው።የአማራ፣የአገው፣የኦሮሞና የሌሎች ብሔረሰቦች በጋራ የሚኖሩበት ክልል ነው።
 
==የተፈጥሮ ሀብት==
በክልሉ አልፎ አልፎ ከሚታዩ የመንግሥትና የማኅበራት ደኖች፣ በደሴቶች፣በአብያተ ክርስቲያናት፣ በወንዞች ዳርቻና ሰው ሊደርስባቸው በማይችሉ ገደላማና ተራራማ ስፍራዎች ከሚገኙ ጥቂት ደኖች በስተቀር ሊጠቀስ የሚችል ከፍተኛ የደን ሀብት ጋር በቅርብ የተያያዘ ነው። በዚህ ረገድ በሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ የሚገኙ እንደ [[ቀይ ቀበሮ]]፣ [[ዋልያ]]፣ [[ጭላዳ ዝንጀሮ]] እንዲሁም በምዕራባዊው የክልሉ አካባቢ [[ዝሆን]] [[አንበሳ]]ና [[ነብር]]፣ [[ሰጐን]]ና የተለያዩ አዕዋፋት በስተቀር ከፍተኛ የዱር እንስሳት ክምችት ካለመኖሩም በላይ በተለያዩ አካባቢዎች ባሉ ጥቂት የደን ቅሪቶችና ዋሻዎች የነበሩት አነስተኛ ቁጥር ያላቸው አራዊቶችም ለዘመናት በደረሰው የደን መጨፍጨፍና መራቆት ምክንያት ከክልሉ ወደ ሌላ አካባቢ እንደተሰደዱ ይታወቃል።
 
የክልሉን የማዕድን ሀብት አስመልክቶ በሚገባ የተጠናከረ ጥናት ባይኖርም ከክልሉ ስነ-ምድራዊ ሁኔታዎችና ከተካሄዱ አንዳንድ ጠቋሚ ጥናቶች መረዳት እንደሚቻለው በክልሉ ውስጥ የተለያዩ ማዕድናት እንደአሉ ይገመታል። በዚህም መሠረት በ[[ሰሜን ሸዋ]] የኦፓል ማዕድን፣ በ[[ሰሜን ጐንደር]]፣ በ[[ጭልጋ]]ና በ[[ደቡብ ወሎ]] በ[[አምባሰል ወረዳ]] የድንጋይ ከሰል ክምችት እንዳሉ መረጃዎች ይጠቁማሉ። ከዚህም በተጨማሪ ለግንባታ ሥራ የሚውል በቂ የድንጋይ፣ የኖራ ድንጋይ፣የሸክላ አፈር፣ ጅኘሲየም፣ የጌጣጌጥ ማዕድናት እንዲሁም በዓባይ ሸለቆ የዕብነ በረድ ሐብቶች እንዳሉ ጥናቶች ይጠቁማሉ። ይሁን እንጅ በውል የሚታወቀው ሐብትም ቢሆን በበቂ ሁኔታ አልለማም።
 
==የውሀ ሀብት==
ክልሉ የትልልቅ ወንዞች ባለቤት ሲሆን በአጠቃላይ በሦስት ዋና ዋና ተፋሰሶች ተከፋፍሎ ሊታይ የሚችል ነው። እነርሱም የ[[ዓባይ]]፣ የ[[ተከዜ]] እና የ[[አዋሽ ወንዝ|አዋሽ]] ተፋሰስ ናቸው። ወደነዚህ ተፋሰሶች የሚገቡና ዓመቱን በሙሉ የማይደርቁ ቁጥራቸው በርካታ የሆኑ ትልልቅ ወንዞች ያሉ ሲሆን በክልሉ በጥቅም ላይ ያልዋለ ሰፊ የውሐ ሀብት መኖሩን ያመለክታሉ። ከነዚህ በተጨማሪ እንደ ጣናና አርዲቦ የመሳሰሉ ሐይቆችም በክልሉ ውስጥ ይገኛሉ። በአጠቃላይ በክልሉ ውስጥ ባሉ ትልልቅ ወንዞችና መጋቢ ወንዞች የመስኖ ልማት ለማካሄድ የሚያስችል ከፍተኛ የውሐ ሐብት ክምችት እንዳለ መገንዘብ ይቻላል። ይሁን እንጅ እስከ አሁን ጥቅም ላይ የዋለው በጣም አነስተኛ ነው።
 
==ምጣኔ ሀብት==
በአመዛኙ አብዛኛው የክልሉ ምጣኔ ሀብት በግብርና እና ከብት እርባታ ላይ የተመሠረተ ነው። በአጠቃላይ ክልሉ ከፍተኛ የሆነ የሕዝብ ቁጥር፣ ለእርሻና ለእንስሳት እርባታ ተስማሚ የሆነ መሬት፣ የአየር ንብረት እና የውሐ ሀብቶች ያሉት በመሆኑ በተለይም የሰብል እና የእንስሳት ሀብት ልማት ለማካሄድ የማይናቅ አቅም አለው። በዝናብም ሆነ የመስኖ እርሻ ልማት በማስፋፋት በክልሉ በገበያ የሚውሉ የተለያዩ የአገዳ፣ የጥራጥሬ፣ የቅባት፣የአትክልትና ፍራፍሬ ሰብሎችን ማምረት ይቻላል። ጤፍ፣ ገብስ፣በቆሎ፣ ማሽላ፣ዳጉሣ፣ ስንዴ፣አተር፣ ባቄላ፣ ሽምብራ፣ ጓያ፣ምስር፣ሰሊጥ፣ ጥጥ፣ ተልባ፣ ወዘተ የመሳሰሉት በክልሉ ውስጥ ከሚመረቱ ሰብሎች መካከል ዋና ዋናዎቹ ናቸው። በእንስሳት ሀብት ረገድም በወተት ምርታማነታቸው የታወቁ የፎገራ ዝርያዎችና በፀጉር ምርት የታወቁት የመንዝ በግ ዝርያዎች በክልሉ ይገኛሉ።
 
==የጎብኚዎች መስሕብ==
በቱሪዝም የሥራ መስክ ሊበለጽጉ ፣በሰፊው አገልግሎት ሊሰጡ የሚችሉ እና በዓለም የቅርስ መዝገብ የሰፈሩት የጐንደር ቤተ መንስግት ህንፃዎች፣ የ[[ላሊበላ]] አብያተ ክርስቲያናት፣ የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ እንዲሁም ልዩ ልዩ የቱሪዝም መስሕቦች አሉት፣ ይሁን እንጅ ክልሉ ሰፊ የሆነ የቱሪዝም እምቅ ሀብት ያለው ቢሆንም በሚፈለገው መጠን በጥቅም ላይ ውሏል ማለት አያስደፍርም። በዚህ ረገድ፤አካባቢዉ የብዙ ታሪካዊ ገዳማትና የታሪካዊ ቅርሶችም ባለሀብት ነው። ለምሳሌ ከሚጠቀሱት መኃል ፦ አደል ሚካኤል፡ ይስር ፏፏቴ፡ ባንጃ ተራራው ወዘተ...
 
==ዋቢ ምንጭ==
[http://www.amharainfo.gov.et/index.html/index.php?option=com_content&view=article&id=61%3A2011-02-10-05-51-55&catid=7%3Aoverview-of-the-region&Itemid=29&lang=en በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ድረ-ገጽ፤ «የክልሉ አጠቃላይ ገጽታ»] በ21 Dec 2012 እ.ኤ.አ. የተቃኘ
{{reflist}}
 
{{የኢትዮጵያ_መረጃ}}
{{መዋቅር}}
 
[[መደብ:የኢትዮጵያ ክልሎች]]
[[መደብ:አማራ ክልል|*]]