ከ«የአክሬ ሪፐብሊክ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
No edit summary
መስመር፡ 35፦
}}
 
'''የአክሬ ረፐብሊክ''' ([[ፖርቱጊዝኛ]]፦ República do Acre), ( [[እስፓንኛ]]፦ República del Acre) ወይም የአክሬ ነፃ መንግሥት (ፖርቱጊዝኛ፦ Estado Independente do Acre), (እስፓንኛ፦ Estado Independiente del Acre) የዛኔ የ[[ቦሊቪያ]] ግዛት በነበረችው በ[[አክሬ ክፍላገር]] ውስጥ የታወጁት ሦስት ተከታታይ ተገንጣይ መንግሥታት ነበሩ። እነዚህም ሦስቱ ተገንጣይ መንግሥታት ከ1891ከ[[1891]] እስከ [[1896]] ዓ.ም ድረስ ባሉት ዓመታት ውስጥ የቆሙት ናቸው። በ1896 ዓ.ም. ክፍላገሩ በይፋ ወደ [[ብራዚል]] ተጨመረችና እሳካሁን የብራዚል አክሬ ክፍላገር ትባላለች። 
 
== ታሪክ ==
መስመር፡ 41፦
ከ1850 ዓም ያህል ጀምሮ፣ ክፍላገሩ በ[[ጎማ]] ኢንዱስትሪ ማዳበሩ ምክንያት በ፵ ዓመታት ውስጥ በብራዚል ዜጎች ተሞልቶ ነበር።<ref>{{መለጠፊያ:Cite book|title=The Amazon Rubber Boom, 1850-1920|last=Weinstein|first=Barbara|year=1983|publisher=Stanford University Press|location=Stanford, CA|isbn=0-8047-1168-2|pages=205}}</ref> በ1860 ዓም [[የአያቹኮ ስምምነት]] ክፍላገሪቱ የቦሊቪያ ግዛት መሆንዋን አረጋግጦ ነበር።
 
ከ1881 ጀምሮ ፖርቱጊዝኛ ተናጋሪዎች የሆኑት የብራዚል ሰዎች የአክሬ ኗሪዎች ብዛት ሆነው፣ ከቦሊቪያ ለመገንጠልና ትንሽ ጊዜ ሳያልፍ ወደ ብራዚል እንዲጨመር የሚለውን ዕቅድ ያሥቡ ጀመር። በ1891 ዓም [[ሉዊስ ጋልቬዝ ሮድሪጌዝ ደ አሪያስ]] እሱም የ[[እስፓንያ]] ዜጋና ጋዜጠኛ ሲሆን አንድ ሠልፍ በዘመቻ ከብራዚል ወደ አክሬ መራ እና በሐምሌ 1891 ዓም «የአክሬ ሪፐብሊክ» ፕሬዚዳንት መሆኑን በአዋጅ አሳወቀ። ሪፐብሊኩን በቅርቡ ከብራዚል ጋራ ለማዋሐድ ያሠበው ቢሆንም፣ በሚከተለው መጋቢት [[1892]] ዓም ግን የብራዚል መንግሥት ሥራዊቱን ልኮ ጋልቬዝን አሠረና ክፍላገሪቱን ወደ ቦሊቪያ ሥልጣን መለሡዋት። ጋልቬዝ ወደ እስፓንያ በስደት ተመለሠና ለግዜው የአክሬ ኗሪዎች ከቦሊቪያም ሆነ ከብራዚል መንግሥታት መቃወም ያገኙ ነበር።
 
በኅዳር [[1893]] ዓም ሁለተኛ ሞክረው የአክሬ ኗሪዎች ሁለተኛ «የአክሬ ሪፐብሊክ» አዋጁ፤ [[ሮድሪጎ ደ ካርቫዮ]] ፕሬዚደንት ተደረገ። ሆኖም እንቅስቃሴው ዳግመኛ ስለ ተቃወመ ለአንድ ወር ብቻ ቆየና አክሬ የቦሊቪያ ግዛት ሆና ቀረች።
 
[[ስዕል:Placido1.jpg|left|thumb|ሆዜ ፕላሲዶ ዴ ካስትሮ]]
ከዚያ በኋላ የአክሬ ሕዝብ አለቃ ወታደሩ [[ሆዜ ፕላሲዶ ዴ ካስትሮ]] ሆነ። እሱ የ30,000 ሰዎች አብዮታዊ ሠራዊት አሠለፈ፤ በአክሬ አብዮት ([[1894]] ዓም) ብዙ ውግያዎች ያሸንፍ ነበር። በጥር [[1895]] ዓም ፕላሲዶ ሦስተኛውን «የአክሬ ሪፐብሊክ» አዋጀ። ከዚሁ ሁናቴ የተነሣ ከአገራት መካከል የሆነ ሁከት ሊሆን መሠለ።
 
በመጨረሻ በኅዳር 1896 ዓም በተዋዋለው በ[[ፔትሮፖሊስ ስምምነት]] ዘንድ፣ ቦሊቪያ ይግባኝ ማለቱን ለብራዚል ለ፪ ሚሊዮን [[ፓውንድ]] በመለዋወጥ ሸጠው። ከዚያ ውል ጀምሮ እስካሁንም ድረስ አክሬ የብራዚል ክፍላገር ሆናለች።