ከ«የአክሬ ሪፐብሊክ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
መስመር፡ 41፦
ከ1850 ዓም ያህል ጀምሮ፣ ክፍላገሩ በ[[ጎማ]] ኢንዱስትሪ ማዳበሩ ምክንያት በ፵ ዓመታት ውስጥ በብራዚል ዜጎች ተሞልቶ ነበር።<ref>{{መለጠፊያ:Cite book|title=The Amazon Rubber Boom, 1850-1920|last=Weinstein|first=Barbara|year=1983|publisher=Stanford University Press|location=Stanford, CA|isbn=0-8047-1168-2|pages=205}}</ref> በ1860 ዓም [[የአያቹኮ ስምምነት]] ክፍላገሪቱ የቦሊቪያ ግዛት መሆንዋን አረጋግጦ ነበር።
 
ከ1881 ጀምሮ ፖርቱጊዝኛ ተናጋሪዎች የሆኑት የብራዚል ሰዎች የአክሬ ኗሪዎች ብዛት ሆነው፣ ከቦሊቪያ ለመገንጠልና ትንሽ ጊዜ ሳያልፍ ወደ ብራዚል እንዲጨመር የሚለውን ዕቅድ ያሥቡ ጀመር። በ1891 ዓም [[ሉዊስ ጋልቬዝ ሮድሪጌዝ ደ አሪያስ]] እሱም የ[[እስፓንያ]] ዜጋና ጋዜጠኛ ሲሆን አንድ ሠልፍ በዘመቻ ከብራዚል ወደ አክሬ መራ እና በሐምሌ 1891 ዓም «የአክሬ ሪፐብሊክ» ፕሬዚዳንት መሆኑን በአዋጅ አሳወቀ። ከትንሽሪፐብሊኩን በኋላ ሪፐብሊኩንበቅርቡ ከብራዚል ጋራ ለማዋሐድ ያሠበው ቢሆንም፣ በሚከተለው መጋቢት 1892 ዓም ግን የብራዚል መንግሥት ሥራዊቱን ልኮ ጋልቬዝን አሠረና ክፍላገሩን ወደ ቦሊቪያ ሥልጣን መለሡት። ጋልቬዝ ወደ እስፓንያ በስደት ተመለሠና ለግዜው የአክሬ ኗሪዎች ከቦሊቪያም ሆነ ከብራዚል መንግሥታት መቃወም ያገኙ ነበር።
 
በኅዳር 1893 ዓም ሁለተኛ ሞክረው የአክሬ ኗሪዎች ሁለተኛ «የአክሬ ሪፐብሊክ» አዋጁ፤ [[ሮድሪጎ ደ ካርቫዮ]] ፕሬዚደንት ተደረገ። ሆኖም እንቅስቃሴው ዳግመኛ ስለ ተቃወመ ለአንድ ወር ብቻ ቆየና አክሬ የቦሊቪያ ግዛት ሆና ቀረች።