ከ«ኣበራ ሞላ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
Content deleted Content added
መስመር፡ 138፦
ዶ/ር ኣበራ ዕድል ባገኙ ቍጥር ችሎታቸውን ለሌሎች ከማስተማርና ስለሚያውቁት ከማስረዳት ኣይቆጠቡም። ለምሳሌ ያህል በቅርቡ ከኣንድ የዋሽንግተን ዲ.ሲ. ሬድዮ ጣቢያ ጋር ስለ ጥሬ ሥጋ ገለጻ ኣድርገው ነበር። ኢትዮጵያውያን ጥሬ ሥጋ ከሚበሉ ሕዝቦች መካከል ስለሆኑ ኣትብሉ ማለት ብቻ ትክክል ስላልሆነ የሚያዋጣው በምርምር የተደገፉ መረጃዎችን ማቅረብ ነው። በኣሁኑ ጊዜ ኢትዮጵያ ውስጥ እንደሚደረገው ከብት በየቦታው እየታረደ ይበላ ስለነበረ ኣሜሪካ ውስጥ እንዲቀር ተወስኖ በ፲፰፻፺፱ ዓ.ም. ፌዴራል ድንጋጌ የኣልተመረመረና ንጹህ ያልሆነ ሥጋ ለሕዝብ ማቅረብ ክልክል ነው። [http://www.fsis.usda.gov/wps/portal/fsis/topics/rulemaking/federal-meat-inspection-act] ሕጉን ኣለማወቅ መከላከያ ኣይደለም። ሥጋው የተመረመረ ለመሆኑ ማሕተሙን ማየት ያስፈልጋል። እንዲህም ሆኖ ኣንድ ሰው የእራሱን እንሰሳት ኣሳድጎና ኣርዶ ሳያስመረምር ቤተሰቡን የማብላት መብት ኣለው።
ጥሬ ሥጋ ጀርሞች ኣሉት። የሚከተሉትንም ማወቅ ጠቃሚ ነው። [https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%A0%E1%88%AC#.E1.8B.A8.E1.89.A0.E1.88.AC_.E1.8C.A8.E1.8C.93.E1.88.AB] ፩. ኣንድ እንሰሳ ሲታረድና ቆዳው ሲገፈፍ ጀርሞች በተለያዩ ሁኔታዎች ሥጋው ውጭ ላይ ስለሚቀሩ ያንን ማስወገድ ኣይቻልም። ፪. እንደ ባክቴሪያ ያሉ ጀርሞች በእየ20 ደቂቃዎች ሁለት በመሆን ይራባሉ። ይኸን እርባታ ቅዝቃዜ ያዘገየዋል። ስለዚህ እንሰሳው እንደታረደ ሥጋው ጥቅም ላይ
፬. ሥጋ ውስጡ ንጹህ ነው። ፭. እንጨት ልሙጥ ስላልሆነ ለጀርሞች መደበቂያ ስለሚያገለግል ለብዙ ሰዎች የሚቀርብ ሥጋ ሲዘጋጅ መክተፊያ፣ የቢላ አጀታና ማቅረቢያው እንጨት ባይሆን ይመረጣል።
===ግዕዝኤዲት ለኣይፎን 6 እና ኣይፓድ===
|