ከ«ኣበራ ሞላ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
መስመር፡ 114፦
ፕ/ር [[እንድርያስ እሸቴ]]፣ [[የኣክሱም ሓውልት ኣስመላሽ ኮሚቴ]]፣ የኢትዮጵያ መንግሥትና ሕዝብ፣ ኣቶ ኃብተኣብ ባይሩ፣ ፕ/ር ሳሙኤል ኣሰፋ፣ ኣቶ ዳዊት ዮሓንስ፣ የኢትዮጵያ ፓርላማ፣ ፕ/ር [[ባሕሩ ዘውዴ]]፣ ማርኮ ቪጎኒ፣ የትግራይ ክልል ፓርላማ፣ ቶኒ ሂኬይ፣ ናፍታለም ኪሮስ፣ እስቲፈን ቤል፣ ኣልበርቶ ኢምፔሪያሊ፣ የሮም ኢትዮጵያውን፣ ጃራ ኃይለማርያም፣ ክቡር ኣቶ ወልደሚካኤል ጫሙ፣ ክቡር ኣቶ [[ሥዩም መስፍን]]፣ ፕ/ር ፍራንካቪግሊያ፣ [[በላይ ግደይ]]፣ ዶ/ር ተቀዳ ዓለሙ፣ ፕ/ር ኣበበ ከበደ፣ ክቡር ኣቶ ተሾመ ቶጋ፣ ጆርጅዮ ክሮቺ፣ የታዋቂ ኢትዮጵያውያን ፊርማ፣ ፲፬ሺህ ፊርማ የፈረሙ የኣክሱም ሕዝቦችና ብዙ ሺህ ፊርማ ያለው በዓለም ላይ ያሉ ኢትዮጵያውያና የጥያቄ ፊርማ (ፔቲሽን)፣ የጥቂት ኣፍሪቃ ኣገሮች ኣምባሳደሮች ደብዳቤዎችና ሌሎችንም ጠቅሷል። ስለ ፊርማውም በማሰማት የቢቢስ ሬድዮና ቴሌቪዥን፣ የካናድ ሬድዮ፣ የእንንግሊዝ፣ የጣልያንና ኣንዳንድ የዓለም ጋዜጣዎች ትኩረት በመስጠት ረድተዋል። ኣንድ ቪድዮም ተሠርቶ ነበር። እዚህ የቀረበው በስም የተጠቀሱትን ብቻ ስለሆነ ወደፊት ማሟላት ይቻላል። ከእዚህ ሁሉ ድካም በኋላ ጣልያኖች ሓውልቱን እንደሚመልሱ ቃል ገብተው በ፲፱፻፺ ዓ.ም. ይመለሳል ተብሎ የጣልያን ፕሬዚደንት ኢትዮጵያን ሲጎበኙ ይቅርታ ከጠየቁም በኋላ የመመለሱ ጉዳዩ በወሬ ቀረ። [http://lubbockonline.com/stories/122698/LA0527.shtml] [http://web.peacelink.it/afrinews/75_issue/p11.html] [http://zoomata.com/archive/italians-protest-return-of-axum-obelisk/#comments] [http://lists.peacelink.it/africa/msg02263.htm] እንዲህም ሆኖ ሓውልቱ እንዲመለስ የደገፉ ጣልያኖች ነበሩ። የጣልያን መንግሥት ለመመለስ ፈቃደኛ ስላልነበረ ተስፋ ተቆርጦ ነበር። የሓውልቱ መመለስ ጉዳይ እንደገና ያንሰራራው ጣልያኖች ሓውልቱን ሮም ሲተክሉት ብረት ኣስገቡበት እንጂ ከመብረቅ ስላልተከላከሉለት ግንቦት ፲፯ ቀን ፲፱፻፺፬ ዓ.ም. መብረቅ ከመታውና ከላይ በኩል ተሰብሮ ከተጎዳ በኋላ ነበር። [http://www.unspecial.org/UNS641/t91.html] [http://news.bbc.co.uk/2/hi/africa/2016098.stm] ምክንያቱም ሌላ መብረቅ ቢመታው ሓውልት መሆኑ ቀርቶ የድንጋይ ክምር ሊሆን ስለሚችል ከልመና ያለፈ እርምጃ በኣንዳችን መወሰድ ስለነበረበት ነው። የሚያሳዝነው ግን ሓውልቱ መብረቅ ከመታውም በኋላ እንኳን ለኢትዮጵያ እንዳይመለስ ተቋውሞ መቀጠል ነበር። [http://news.bbc.co.uk/2/hi/europe/2119400.stm] [http://zoomata.com/archive/italians-protest-return-of-axum-obelisk/#comments]
 
ከእዚህ በላይ ለተዘረዘሩትና ሌሎችም ለኢትዮጵያ ስለ ኣደረጉት ኣስተዋጽዖ በተለይ ለፕሮፌሰር ፓንክኸረስት እግዜር ውለታቸውን ይስጥልን። [http://ethiopianamericanforum.com/index.php?option=com_content&view=article&id=257:aksum-obelisk-revisited] ጣልያኖች የ[[ኣድዋ]]ን ድል ለመበቀልና [https://www.youtube.com/watch?v=2Itp4xvDNgc&feature=player_embedded] ኢትዮጵያ በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ጣልያንን ለሁለተኛ ጊዜ ስለ ኣሸነፈች ተበሳጭችተው ሓውልቱ ላይ ቢንጠላጠሉም [http://web.peacelink.it/afrinews/75_issue/p11.html] ከኣክሱም የወሰዱትን ሓውልት ሌላ ትውልድ ኣስመልሷል። [http://ethiopiaonline.net/obelisk/] [http://www.linkethiopia.org/guide-to-ethiopia/the-pankhurst-history-library/dr-vincenzo-francaviglia-and-the-re-erection-of-the-great-aksum-obelisk/] [http://www.tadias.com/08/02/2008/pankhursts-memories-of-the-aksum-obelisk-issue/] [http://nazret.com/blog/index.php/2008/09/07/ethiopia_axum_town_residents_award_meles] [http://ethiopianamericanforum.com/index.php?view=article&id=671:december-30-2013&tmpl=component&print=1&page=] [http://books.google.com/books?id=KvXpBAAAQBAJ&pg=PT765&lpg=PT765&dq=Dr.+Aberra+Molla&source=bl&ots=--zz8kODT4&sig=MG0ZrM5LLBxEW_wYdK-iYl6rZmM&hl=en&sa=X&ei=VOxTVLSiJoilyQTvt4CoCg&ved=0CC4Q6AEwAzge#v=onepage&q=Dr.%20Aberra%20Molla&f=false] ታሪኩ እንዳይጠፋ ኣንድ ቦታ መጻፍ ተገቢ ነው። የዓለም ቅርስ እንጂ ጉራም ኣይደለም። [http://whc.unesco.org/en/list/15] ይህ ሲደረግም በየተባበሩት መንግሥታት ስምምነት መሠረት ይኸን ትልቅ ቅርሷን [http://www.africanidea.org/magnificent_aksum.html] ለማስመለስ ለዓመታት ስትታገል ኢትዮጵያን የረዳት መንግሥት ኣልነበረም። [http://www.ethioscoop.com/ethiopian-articles/3818-obelisk-of-axum.html] [http://www.abovetopsecret.com/forum/thread377718/pg1] የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት የሳይንስና የባህል ድርጅት እንኳን ሓውልቱን መብረቅ ከመታው በኋላ ለኢትዮጵያ ይመለስ ኣላለም። [http://web.peacelink.it/afrinews/75_issue/p11.html] ማንም ኣያስገድደንም ብለው የዓለም ሕዝብ ላይ ሲቀልዱ የነበሩትን ጣልያኖች [http://articles.baltimoresun.com/2001-08-05/news/0108040051_1_obelisk-ethiopians-mussolini] ኣንድ ሰው ሊያስመልሰውና እንደሚዋረዱ ኣስጠንቅቆ ሓውልቱን ከማስመለስ በስተጀርባ ትምህርትነትም ኣሉት። ጣልያኖች የኣክሱምን ሓውልት ዘርፈው ከ፷፱ ዓመታት በኋላ በ፲፱፻፺፰ ዓ.ም. የመለሱት እንዳይዋረዱ እንጂ ወድደው ኣይደለም። [http://am.advisor.travel/poi/yaakesume-hhawelete-18986] ጣልያኖች የተሰጣቸውን በጎ ፈቃድ [http://www.ethiopic.com/heritage/aksum.htm] ተጠቅመው ሓውልቱን ቢመልሱም በፈቃዳችን መለስን ብለው ሸንግለዋል። [http://www.thefreelibrary.com/Ethiopia%3A+no+plane+to+carry+obelisk+home%3F+After+50+years+of+broken...-a0119650209] [http://www.theguardian.com/world/2004/jul/16/italy.artsnews] [http://www.theguardian.com/world/2004/jul/16/italy.artsnews] [http://www.unesco.org/new/en/unesco/partners-donors/the-actions/culture/resettlement-of-aksum-obelisk/] [http://rome.wantedworldwide.net/news/372/axum-obelisk.html] [http://news.bbc.co.uk/2/hi/africa/4458105.stm#graphic] ከእዚያም ወዲህ ከዘረፏቸው መካከል እንኳን በፈቃዳቸው ተለምነውም ለኢትዮጵያ የመለሱት ሌላ ቅርስ የለም። [http://www.thefreelibrary.com/Ethiopia%3A+no+plane+to+carry+obelisk+home%3F+After+50+years+of+broken...-a0119650209] ጣልያኖች በ፳፻፪ ዓ.ም. ለግራዚያኒ ሓውልት ስለሠሩ ከታሪክ መማር ሳይጠቅመን ኣይቀርም። [http://www.goolgule.com/open-letter-to-italian-minister-of-foreign-affairs/] [http://www.africanidea.org/Repoublic_prato.html] [http://www.bbc.com/news/world-europe-19267099] [http://www.unesco.org/culture/laws/pdf/abstract_scovazzi.pdf] [http://ethiomedia.com/101facts/adwa_speech_denver_2015.pdf]
 
በቅርቡም ጄፍ ፒይርስ (Jeff Pierce) የተባሉ ደራሲ ስለ ኢትዮጵያውያን ጀግንነትና ጣልያንን ለሁለተኛ ጊዜ በማሸነፍ ዓለምን እንደቀየሯት በጻፉት PREVAIL (ISBN: 978-1-62914-528-0 አና ISBN: 978-1-63220-096-9) መጽሓፋቸው የኢትዮጵያን በደል የማይረሱ ዛሬም እንዳሉ በማሳሰብ ስለ ኣክሱም ሓውልት ወደ ኢትዮጵያ መመለስ ሲያሰፍሩ ዶክተሩን (Dr. Aberra Molla) ገጽ 552 ላይ ጠቅሰዋል። [https://books.google.com/books?id=KvXpBAAAQBAJ&pg=PT2&lpg=PT2&dq=ISBN+978-1-62914-528-0&source=bl&ots=--Ay1fOIY8&sig=QiEnbnh4onJiwBrpgZDyx5iJG-c&hl=en&sa=X&ei=DdHRVJXiOcOxggTcoICoCA&ved=0CCAQ6AEwAA#v=onepage&q=ISBN%20978-1-62914-528-0&f=false] [https://www.facebook.com/ethiopianwar/photos/pb.258347827654138.-2207520000.1423036901./268727979949456/?type=3&theater] [https://www.facebook.com/ethiopianwar] [https://books.google.com/books?id=KvXpBAAAQBAJ&pg=PT765&lpg=PT765&dq=Prevail+Pierce+Aberra+Molla&source=bl&ots=--Az3cJCT6&sig=v7MzpEfs61qkFwHBXCKGD9meR7A&hl=en&sa=X&ei=SpXjVKCyBpSoyASI7YDYAQ&ved=0CDcQ6AEwBA#v=onepage&q=Prevail%20Pierce%20Aberra%20Molla&f=false] [https://www.facebook.com/GeezEdit] [http://www.ethiopia.org/index.php?option=com_content&view=article&id=149:prevail-by-jeff-pearce&catid=14&lang=en] [http://ethsat.com/video/esat-yesamintu-engida-dr-abera-molla-february-2015/] [http://www.prweb.com/releases/2013/2/prweb10436175.htm][http://am.advisor.travel/poi/yaakesume-hhawelete-18986] [http://ethiomedia.com/101facts/adwa_speech_denver_2015.pdf]