ከ«ሙት-አሽኩር» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
No edit summary
መስመር፡ 1፦
'''ሙት-አሽኩር''' [[አሞራዊው]] የ[[አሦር]] ንጉሥ [[1 እሽመ-ዳጋን]] ልጅና ተከታይ ነበረ።
 
በእሽመ-ዳጋን ዘመን የ[[ሑራውያን]] ጎሣ የ[[ቱሩካውያን]] ንጉሥ ዛዚያ በስምምነት ሴት ልጁን ለሙት-አሽኩር አጋባት። እሽመ-ዳጋን ባረፈው ጊዜ (ምናልባት 1678 ዓክልበ.) ብዙ ሌሎች ሰዎች ለአሦር ንጉሥነት ተነስተው ብሐራዊ ጦርነት እንደ ሆነ ይመስላል። የሙት-አሽኩር ስም በ''[[የአሦር ነገሥታት ዝርዝር||አሦር ነገሥታት ዝርዝር]]'' አይገኝም፣ ዳሩ ግን በእርሱ ፈንታ ስለ [[አሹር -ዱጉል]]፦ «አሹር-ዱጉል ዲቃላ ልጅ ነበረ፣ የዙፋን ማዕረግ አልነበረውም። በአሹር-ዱጉል ዘመን መጀመርያ፣ 6 ሌሎች «ዲቃላ» የተባሉ ጣውንት ነገሥታት ተነሡ፦ አሹር-አፕላ-ኢዲ፣ ናሲር-ሲን፣ ሲን-ናሚር፣ ኢፕቂ-ኢሽታር፣ አዳድ-ሳሉሉ እና [[አዳሲ]] ናቸው።»
 
ከዚህ በላይ በዚህ ወቅት የ[[ባቢሎን]] (የ[[ሃሙራቢ]]) አገረ ገዥ ፑዙር-ሲን ንጉሡን [[አሲኑም]] (የሻምሺ-አዳድ ልጅ-ልጅ) [[አሞራዊ]] ስለ ነበር ከዙፋኑ እንዳባረረው በማለት አስቀረጸ።