ከ«ሹልጊ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
No edit summary
መስመር፡ 28፦
በሌሎች ምንጮች ግን ሹልጊ እንደ ጽድቅ ንጉሥ አልታሠበም። «[[የዋይድነር ዜና መዋዕል]]» (ABC 19) የሚባል ሰነድ «ሥርዓቶቹን በትክክል አልፈጸመም፤ የማጽዳቱንም ሥርዓተ ቅዳሴ አረኮሰ» ሲለን CM 48 ሥርዓቶቹን በማይገባ እንደ ቀየራቸው፣ «ሀሣዌ ጽሁፎች» እንደ ቀረጸ በማለት ይከሰዋል። «[[የቀድሞ ነገሥታት ዜና መዋዕል]]» (ABC 20) ደግሞ «የወንጀል አመል ነበረው፤ የ[[ባቢሎን]]ም መቅደስ ንብረት እንደ ምርኮ ወሰደ» የሚል ክስ አቀረበበት።
 
በመጀመርያ ዓመቶቹ የዓመት ስሞች በተለይ መቅደሶች ስለ መሥራታቸው ሲሆን ከተሠሩባቸው ከተሞች መሃል ደር አንዱ ነበር። በ፳ኛው ዓመት ግን «የደር ሂሳብ በዶማዎች እንዲከፈል» አዝዞ ከተማውን በቅጣት አስፈረሰው። ከዚያ የዘመተባቸው ቦታዎች በ[[ሆራውያንሑራውያን]] አገር፣ በሉሉቢ ወይም በ[[ኤላም]] ነበሩ። በ፴ኛው ዓመቱ ሴት ልጁ የአንሻን አገረ ገዥ ብታገባም በ፴፬ኛውም ዓመቱ ግን በአንሻን ላይ የቅጣት ዘመቻ እየዘመተ ነበር።
 
የሹልጊ ተከታይ ልጁ [[አማር-ሲን]] ነበር።