ከ«1 ሰኑስረት» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
Robot-assisted disambiguation: ከነዓን - Changed link(s) to ከነዓን (ጥንታዊ አገር)
 
መስመር፡ 16፦
በ፲ኛውና በ፲፰ኛው ዓመት በ[[ኩሽ መንግሥት]] ላይ እንደ ዘመተ ይታወቃል። ሆኖም ሰኑስረት በአባቱ በ፩ አመነምሃት ፳ኛው ዓመት (1982 ዓክልበ. ግድም) በጋርዮሽ ዘውዱን ስለ ተጫነው፤ መጀመርያው ዓመቱ ከዚያ ይቆጠራል። ስለዚህ በኩሽ ላይ የዘመቱ በ1972ና በ1964 ዓክልበ. ግድም ይሆናል። የግብጽ ደቡብ ጠረፍ ከኩሽ ጋራ ከ[[የአባይ ሙላቶች|፩ኛው ሙላት]] እስከ ፪ኛው ሙላት አስፋፋው።<ref>[http://www.touregypt.net/featurestories/senusret1.htm Senusret I] {{en}}</ref> በተጨማሪ ሎሌዎችን ወደ [[ሲና]] ልሳነ ምድር ለማዕድን እንደ ላከ ይታወቃል።
 
''[[የሲኑሄ ታሪክ]]'' በተባለው ጽሑፍ ዘንድ፣ አባቱ አመነምሃት በዋና ከተማው በ[[ኢጭታዊ]] እየነገሠ፣ የጋርዮሽም ንጉሥ ኸፐርካሬ ሰኑስረት በ«[[ጤሄኑ]]» ([[ሊብያ]]) እየዘመተ፣ ያንጊዜ በድንገት አመነምሃት ዓረፈ። (ይህ ከሤራ የተነሣ መሆኑ ቢመስልም ግልጽ አይደለም)። ወዲያው ሰኑስረት በአስቸኳይ ወደ ኢጭታዊ ተመለሠ። የሰኑስረት አለቃ ሲኑሄ ግን ወደ ግብጽ እንዳይመለስ ሁከት ፈርቶ እስከ «[[ረጨኑ]]» (ስሜን [[ከነዓን (ጥንታዊ አገር)|ከነዓን]]) ድረስ ይሸሻል። በዚያ ሲኑሄ የረጨኑ አለቃ አሙነንሺ ባለሟልና ጦር አለቃ ሆነ። ከብዙ ዓመታት በኋላ ሲኑሄ ሽማግሌ ሆኖ ወደ አገሩ ወደ ሰኑስረት ግቢ ሲመልስ፣ የ«ፈንቁ» ([[ፊንቄ]]) አለቃ መኑስ እና የ«ቀደም» (?) አለቃ መኪ የፈርዖን ወዳጆች እንደ ሆኑ ይገልጻል። ይህ ጽሑፍ እንደ ልብ ወለድ ቢቆጠረም፣ ታሪካዊ መሠረት መኖሩ የሚከራከር ነው።
 
ሰኑስረት በግብጽ ብዙ ህንጻዎችና መቅደሶች አንዳሠራ ይታወቃል። አሁን በተለይ የሚታወቀው በ[[ካርናክ]] እንደገና ታድሶ የሚታየው «[[ነጭ መቅደስ]]» ነው። ከአማካሪዎቹ መጀመርያው ጠቅላይ ሚኒስትር [[እንተፊቀር]]ና ከዚያ [[ሰኑስረት (አማካሪ)|ሰኑስረት]] ይታወቃሉ፤ እንዲሁም ባጀሮንዱ ሶበክሆተፕና ባጀሮንዱ [[መንቱሆተፕ (ባጀሮንድ)|መንቱሆተፕ]] ይታወቃሉ።