ከ«ነነዌ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
Content deleted Content added
No edit summary |
|||
መስመር፡ 23፦
በ''[[ኦሪት ዘፍጥረት]]'' 10፡11 መሠረት የ[[ሴም]] ልጅ [[አሦር (የሴም ልጅ)|አሦር]] ከ[[ሰናዖር]] ወጥቶ ነነዌንና ሌሎችን ከተሞች ሠራ። አንዳንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉሞች ግን ከፊተኛው ቁጥር ከ10፡10 በመውሰድ አድራጊው እንደ [[ናምሩድ]] ቆጥረውት፣ ናምሩድ እራሱ ወደ አሦር (ወደ ሀገሩ) ወጥቶ እኚህን ከተሞች እንደ ሠራ ይላሉ። በጥንታዊ የ[[ግሪክ (አገር)|ግሪክ]] ታሪክ ጸሃፊዎች ዘንድ [[ኒኑስ]] የነነዌ መስራችና የአሦር መጀመርያ ንጉስ ነበረ።
ነነዌ ከጥንት ጀምሮ ከ[[አሹር (ከተማ)|አሹር]] ከተማ-አገር ይገዛ ነበር። እንደ አሹር ከ1440 እስከ 1366 ዓክልበ. ድረስ በ[[ሚታኒ]] ይቆጣጠር ነበር። ትልቅ ከተማ ነበረ።
በ775 ዓክልበ. አካባቢ ነቢዩ [[ዮናስ]] ወደ ነነዌ ሂዶ የአሦር ሰዎች ወደ ንሥሐ እንዳመጣቸው በ''[[መጽሐፈ ዮናስ]]'' ይገለጻል። የዮናስ መቃብር የሚባለው የተቀደሠ መስጊድ በነነዌ (የአሁኑ [[ሞሱል]]) አካባቢ ይገኝ ነበር፤ በሐምሌ [[2006]] ዓ.ም. የኢስላማዊ ተቃጊዎች ከ«[[ኢስላም ግዛት በኢራቅና ሶርያ]]» ወገን የዮናስን መስጊድ አፈረሱት።
በ713 ዓክልበ. ንጉሥ [[ሰናክሬም]] የአሦርን ዋና ከተማ ወደ ነነዌ መለሠው።
{{መዋቅር-ታሪክ}}
|