ከ«ጥንታዊ ግብፅ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
መስመር፡ 44፦
 
በ2121 ዓክልበ. ግድም አዲስ «ጤባዊ» (፲፩ኛው) ሥርወ መንግሥት በ[[2 መንቱሆተፕ]] ተመሠረተ። ዋና ከተማው [[ጤቤስ]] በደቡብ ሲሆን በስሜኑ በሄራክሌውፖሊስ የነበረው ቀቲዎች ወገን በመሪካሪ መሪነት ዓመጹ። ለጊዜው ሁለቱ ፈርዖኖች — መሪካሬ በስሜንና መንቱሆተፕ በደቡብ — ይታገሉ ነበር። በመጨረሻ ግን መንቱሆተፕ ድል አድርጎ እንደገና መላውን ግብጽ ገዛ። ይህ መንቱሆተፕ የዙፋን ስሙን በየጊዜ የቀየረው ምክንያት ግልጽ ባይሆንም እንደ ቀድሞው ኻሰኸምዊ በመምሰል አዲስ አገር ሲገዛ አዲስ ስም እንዳወጣ ይሆናል። በግብጽ አረመኔ እምነት መንቱሆተፕ ደግሞ የጥንታዊ ጣኦት [[ኦሲሪስ]] ትስብዕት ለብዙ ዘመናት ይቆጠር ነበር።
 
ሦስቱ አንተፎች ([[1 አንተፍ]]፣ [[2 አንተፍ]]ና [[3 አንተፍ]]) በአመጽ ምክንያት ስሜኑን ለመግዛት አልቻሉም። ከጤቤስ ወደ ስሜንም ሆነ ወደ ደቡብ የነበሩት [[የግብጽ ኖሞች]] ገዦች አይቀበሉዋቸውም ነበር። [[3 መንቱሆተፕ]]ና ልጁ [[4 መንቱሆተፕ]] በአጭር ዘመን ውስጥ ይገዙ ነበር። በዚህ 11ኛው (ጤባዊ) ሥርወ መንግሥት መጨረሻ፣ «የግብጽ መካከለኛ መንግሥት» ዘመን መሠረት ይባላል።
 
==መካከለኛው መንግሥት==
 
==ሁለተኛው መካከለኛ ዘመን==
 
==አዲሱ መንግሥት==
 
==ዋቢ ምንጮች==
 
<references/>