ከ«ካሩም» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
No edit summary
መስመር፡ 6፦
ከዚህ ጥቂት ዓመታት በኋላ የ[[አካድ]] ንጉሥ [[ታላቁ ሳርጎን]] ኤብላን አጠፋ። ከኋለኛ ዘመን በ[[ኬጥኛ]] በተጻፈ ታሪክ ዘንድ፣ የ[[ቡሩሻንዳ]] ንጉሥ ኑርዳጋል በ''ካሩሞች'' የነበሩትን አካዳዊና አሦራዊ ነጋዴዎች መደብ ስለ በደለ፣ ሳርጎን ደግሞ አናቶሊያን ወረረ። ይህም ድርሰት በ[[አማርና ደብዳቤዎች]] መካከል በ[[አካድኛ]] ተገኘ፤ ቅጂዎቹ ግን በሳርጎን ዘመን ስላልተጻፉ እንደ ታማኝ ታሪክ አይቆጠሩም።
 
በሐቲ እነዚህ የአሦራውያን ነጋዴ ሠፈሮች ከሐቲ ከተሞች አጠገብ ይመሠረትይመሠረቱ ነበር፤ ቀረጥም ለከተማው ገዢ ያስረክቡ ነበር።<ref>Seton Lloyd : ''Ancient Turkey'' ( Translation: Ender Verinlioğlu) Tubitak, Ankara, 1998 p 18-19</ref> አነስተኛ «መባርቱም» የተባሉት ጣቢያዎች ደግሞ ነበሯቸው። በተለይ 1880-1750 እና 1720-1680 ዓክልበ. በጠቅላላ የ''ካሩም''ና የ''መባርቱም'' ቁጥር ምናልባት ፳ ያሕል ነበር። ከነዚህም ውስጥ [[ካነሽ]]፣ [[አንኩቫ]]፣ [[ሐቱሳሽ]] በዋናነት ይጠቀሳሉ። [[የኬጥያውያን መንግሥት]] ከተነሣ ቀጥሎ ግን ''ካሩሞቹ'' ከአናቶሊያ ጠፉ።
 
በዚሁ ዘመን መደበኛ ገንዘብ (መሀልቅ) ገና አልተፈጠረም ነበር። የአሦር ነጋዴዎች [[ወርቅ]] በጅምላ፣ [[ብር (ብረታብረት)|ብር]] ለችርቻሮ ይጠቅማቸው ነበር። የወርቅ ዋጋ ከብር ፰ እጥፍ መሆኑ ተወሰነ። ሆኖም ሌላ የብረታብረት አይነት በአሦርኛ «አሙቱም» ሲባል ይህ ከወርቅም በላይ ውድ ነበር፤ ከብር ፵ ጊዜ ተላቀ። «አሙቱም» ምናልባት ያንጊዜ ትኩስ ግኝት የነበረ [[ብረት]] ሊሆን ይቻላል። እነዚህ የአሦር ነጋዴዎች በተለይም [[ቆርቆሮ]]ና [[ልብስ]] ለሐቲ ሰዎች ይሸጡ ነበር። ከሐቲ አገር ካስወጡአቸው ውጤቶች መካከል ከሁሉ አይነተኛ የሆነው [[መዳብ]] ነበረ።<ref>Ekrem Akurgal: ''Anadolu Kültür Tarihi'',Tubitak, Ankara,2000 ISBN 975-403-107-X p 40-41</ref>