ከ«1 አመነምሃት» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
No edit summary
መስመር፡ 3፦
አመነምሃት መጀመርያ በነብታዊሬ አጭር ዘመን የነብታዊሬ አለቃ ወይም ሚኒስትር ይመስላል። በቅርብ ጊዜ ውስጥ ይህ አመነምሃት እራሱ ፈርዖን ሆነ። ነብታዊሬ ወዴት እንደ ሄደ ወይም እንደ ኖረ እንዳልኖረ አይታወቅም።
 
አመነምሃት ከ፯ መቶ ያህል ዓመት በፊት ጠፍቶ የነበረውን [[ጥንታዊ መንግሥት]] ለማሳደስ ያደረገው ጥረት ሊታወቅ ችሏል። ይህም በጥንታዊ መንግሥት ፈሊጥ የሆነውን [[ሀረም]] በማስገንባቱ በኩል ይታያል። እንዲሁም ከአመነምሃት ዘመን በ[[ግብጽኛ]] የተጻፈው [[ሥነ ጽሁፍ]] ይህን ሀሣብ ያስረዳል። ከነዚህ መካከል ''[[የአመነምሃት ትምህርት]]''፣ ''[[የሲኑሄ ታሪክ]]'' እና ''[[የነፈርቲ ትምህርትትንቢት]]'' ዋናዎቹ ናቸው።
 
በአመነምሃት ዘመነ መንግሥት በ፳ኛው ዓመት (1982 ዓክልበ. ግድም) ልጁን [[1 ሰኑስረት]]ን ከእርሱ ጋር በጋርዮሽ ወደ ዙፋኑ አስነሣው። በዚህ ዓመት ደግሞ የግብጽ ዋና ከተማ ከ[[ጤቤስ]] ወደ አዲስ ከተማ [[ኢጭታዊ]] አዛወረው።
 
በጽሑፎቹ መሠረት ልጁ ሰኑስረት በ[[ሊብያ]] እየዘመተ አመነምሃት በሤራ እንደ ተገደለ ይታሥባል።
 
==የነፈርቲ ትንቢት==
''የነፈርቲ ትንቢት'' በ፩ አመነምሃት ዘመን የተጻፈ ትውፊት ነው። ትውፊቱ በቀድሞ ዘመን በ[[ጥንታዊው መንግሥት]] [[4ኛው ሥርወ መንግሥት]] በነገሰው በ[[ስነፈሩ]] ዘመን ( ዓክልበ. ግድም) ስለ ኖረ «ነፈርቲ» ስለ ተባለ ቄስ የተመለከተ ነው።
 
ፈርዖኑ ስነፈሩ ሰልችቶት ነፈርቲ ትንቢት እንዲናገርለት አዘዘውና ንጉሡ የተናገረውን ቃል ጻፈው ይላል። ነቢዩ ለስነፈሩ፦ ወደፊት ሀገሩ አዲስ እንዲመሠረት ያስፈልጋል፤ እስከ መጨረሻውም ጥፍር ድረስ በሙሉ ይጠፋል፤ ማንም የሚጠብቃት አይተርፍምም፤ ሆኖም ወደፊት «አመኒ» የሚባል ንጉሥ ነግሦ መንግሥቱን አዲስ ይሠራዋል ብሎ ነበየለት።
 
የዚህ ትውፊት መንስዔ በእርግጡ ሊታወቅ ባይቻለንም ፈርዖኑ «አመነምሃት» የሚለውን የዙፋን ስም መውሰዱን ለማጽደቅ እንደ ታሠበ ይሆናል።
 
<gallery>