ከ«ካሩም» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
አዲስ ገጽ ፈጠረ፦ «thumb|300px|መካከለኛ አናቶሊያ '''ካሩም''' በጥንት (2150-1600 ዓክልበ. ያሕል) የአሦር ሰዎች...»
(No difference)

እትም በ19:36, 18 ፌብሩዌሪ 2014

ካሩም በጥንት (2150-1600 ዓክልበ. ያሕል) የአሦር ሰዎች በውጭ አገራት በተለይ በሐቲ (አናቶሊያ) ያቋቋሙት የንግድ ሠፈሮች ነበሩ።

መካከለኛ አናቶሊያ

ኤብላ ጽላቶች መካከል አንዱ ሰነድ ከኤብላ (በሶርያ) እና ከአሹር (ወይም ከአባርሳል?) መካከል የተዋወለ ውል ሲሆን በዚህ ውል አሹር በኤብላ ግዛት ውስጥ ካሩም ለማስተዳደር ፈቃድ አገኘ።

ከዚህ ጥቂት ዓመታት በኋላ የአካድ ንጉሥ ታላቁ ሳርጎን ኤብላን አጠፋ። ከኋለኛ ዘመን በኬጥኛ በተጻፈ ታሪክ ዘንድ፣ የቡሩሻንዳ ንጉሥ ኑርዳጋል በካሩሞች የነበሩትን አካዳዊና አሦራዊ ነጋዴዎች መደብ ስለ በደለ፣ ሳርጎን ደግሞ አናቶሊያን ወረረ። ይህ ጽላት በሳርጎን ዘመን ስላልተጻፈ ግን እንደ ታማኝ ታሪክ አይቆጠርም።

በሐቲ እነዚህ የአሦራውያን ነጋዴ ሠፈሮች ከሐቲ ከተሞች አጠገብ ይመሠረት ነበር፤ ቀረጥም ለከተማው ገዢ ያስረክቡ ነበር።[1] አነስተኛ «መባርቱም» የተባሉት ጣቢያዎች ደግሞ ነበሯቸው። በጠቅላላ የካሩምና የመባርቱም ቁጥር ምናልባት ፳ ያሕል ነበር። ከነዚህም ውስጥ ካነሽአንኩቫሐቱሳሽ በዋናነት ይጠቀሳሉ። የኬጥያውያን መንግሥት ከተነሣ ቀጥሎ ግን ካሩሞቹ ከአናቶሊያ ጠፉ።

በዚሁ ዘመን መደበኛ ገንዘብ (መሀልቅ) ገና አልተፈጠረም ነበር። የአሦር ነጋዴዎች ወርቅ በጅምላ፣ ብር ለችርቻሮ ይጠቅማቸው ነበር። የወርቅ ዋጋ ከብር ፰ እጥፍ መሆኑ ተወሰነ። ሆኖም ሌላ የብረታብረት አይነት በአሦርኛ «አሙቱም» ሲባል ይህ ከወርቅም በላይ ውድ ነበር፤ ከብር ፵ ጊዜ ተላቀ። «አሙቱም» ምናልባት ያንጊዜ ትኩስ ግኝት የነበረ ብረት ሊሆን ይቻላል። እነዚህ የአሦር ነጋዴዎች በተለይም ቆርቆሮልብስ ለሐቲ ሰዎች ይሸጡ ነበር። ከሐቲ አገር ካስወጡአቸው ውጤቶች መካከል ከሁሉ አይነተኛ የሆነው መዳብ ነበረ።[2]

ዋቢ ምንጮች

  1. ^ Seton Lloyd : Ancient Turkey ( Translation: Ender Verinlioğlu) Tubitak, Ankara, 1998 p 18-19
  2. ^ Ekrem Akurgal: Anadolu Kültür Tarihi,Tubitak, Ankara,2000 ISBN 975-403-107-X p 40-41