ከ«አሹር (ከተማ)» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
ሎሌ፦ መያያዣዎች ወደ 1 ልሳናት አሁን በWikidata ገጽ d:q200200 ስላሉ ተዛውረዋል።
No edit summary
 
መስመር፡ 21፦
'''አሹር''' የ[[አሦር]] ጥንታዊ ዋና ከተማ ነበር። ፍርስራሹ በ[[ጤግሮስ ወንዝ]] ምዕራብ ዳርቻ አሁን ሊታይ ይችላል። «አሹር» የሚለው ስም ደግሞ በ[[አካድኛ]] (አሦርኛ) ማለት የአገሩ አሦር ስም እና የ[[አረመኔ]] ሃይማኖታቸው ዋና ጣኦት [[አሹር (ጣኦት)|አሹር]] ነበር። በ[[ዕብራይስጥ]]ም «አሹር» ማለት ወይም አገሩ ወይም [[አሦር (የሴም ልጅ)|አሦር]] (የ[[ሴም]] ልጅ) ሊሆን ይቻላል።
 
አሹር ከተማ የተሠራው ከ2380 ዓክልበ. አስቀድሞ ይሆናል። በ2115 ዓክልበ. ግ. [[ኢብሉል-ኢል]] «የ[[ማሪ]]ና የአሹር ንጉሥ» ተባለ። ከጥቂት ዓመታት በኋላ (2106 ዓክልበ. ግ.) መጀመርያው አሦራዊ ንጉሥ [[ቱዲያ]] ከ[[ኤብላ]] ሚኒስትር [[ኤብሪዩም]] ጋር ስምምነት እንደ ተዋዋለ ይታወቃል። በ1980 ዓክልበ. ገደማ ጥንታዊው የአሦር ንጉሥ [[ኡሽፒያ]] የአሹር ቤተ መቅደስ መስራች እንደ ነበር ይተረካል። በዚህ ወቅት አሹር የአሦር ከተማ-አገር መቀመጫ ሆነ። [[1 እሽመ-ዳጋን]] በ1678 ዓክልበ. ከሞተ በኋላ የ[[ባቢሎን]] ንጉሥ [[ሃሙራቢ]] ሥልጣን ያዘ፤ የአሹር ነገሥታት ለትንሽ ጊዜ ለባቢሎን ተገዥ ቢሆኑም በይፋ በነፃነት ገዙ። ከ1440 ግድም አሹር በ[[ሚታኒ]] ንጉሥ [[ሻውሽታታር]] ተዘርፎ ከዚያ እስከ 1366 ዓክልበ. ድረስ የአሹር ነገሥታት ለሚታኒ ይገዙ ነበር። በ1366 ዓክልበ. ግን [[1 አሹር-ኡባሊት]] የሚታኒ ሰዎችን አባረራቸውና የአሦር መንግሥት ይስፋፋ ጀመር። በ[[ኒኑርታ-አፒል-ኤኩር]] ዘመን (በ1195 ዓክልበ. ገደማ)፣ አንድ [[የምድር መንቀጥቀጥ]] በአሹር የነበረውን መቅደስ በሙሉ አጠፋው።
 
በ887 ዓክልበ. [[2 አሹር-ናሲር-ፓል]] የአሦርን ዋና ከተማ ከአሹር ወደ [[ካልሁ]] አዛወረው። የአሦር መንግሥት በ622 ዓክልበ. በወደቀበት ጊዜ የአሦር ጠላቶች ባቢሎን፣ [[ሜዶን]]ና [[እስኩቴስ]] ሰዎች አሹርን አጠፉት። ሆኖም በኋላ አዲስ መንደር በሥፍራው ቆሞ እስከ [[14ኛው ክፍለ ዘመን]] ዓ.ም. ድረስ ይቆይ ነበር።