ከ«ፒሬኔ ተራሮች» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
Content deleted Content added
No edit summary |
ጥNo edit summary |
||
መስመር፡ 4፦
==ስያሜ==
[[ዲዮዶሮስ ሲኩሉስ]] (60 ዓክልበ. ግድም) እንደ ጻፈው (V. 35) በጥንት ከእረኞች አለመጠንቀቅ የተነሣ አንድ ታላቅ እሳት ዙሪያውን በሙሉ ስላቃጠለ የተራሮቹ ስም ከ«እሳት» (ፒር ወይም ፑር በ[[ግሪክኛ]]) መጣ። በመቃጠላቸው ምክንያት የ[[ብር (ብረታብረት|ብር (ብረታብረት)|]] ፈሳሾች ተገለጡ። የ[[ፊንቄ]] ሰዎች ሲደርሱ ብር እንደ ርካሽ ዕቃ አገኝተውት ከኗሪዎቹ በንግድ ገዝተውት እንደ በለጠጉ ይለናል።
በኋላ ግን የ[[ሮሜ]] ደራስያን [[ሉካን]] (60 ዓ.ም.) እና [[ሲልዩስ ኢታሊኩስ]] (90 ዓ.ም.) ሌላ ትውፊት ጻፉ። [[ሄርኩሌስ ሊቢኩስ]] የ[[ጌርዮን]]ን ከብት ለመውሰድ እየሄደ የተራሮች አውራጃ ንጉሥ [[ቤብሩክስ]] ጋበዘው። ሄኩሌስ ግን ሰክሮ የንጉሡን ሴት ልጅ [[ፒሬኔ]] በግድ ጠልፎ ከኅፍረቷ በተራሮቹ እስከ መሞቷ ድረስ ተንቀዋለለች። ስምዋን ለተራሮቹ ሰጠች ብለው ጻፉ።
|