ከ«ጉታውያን» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
No edit summary
መስመር፡ 5፦
መጀመርያ በታሪክ መዝገብ የሚታዩ፣ ለ[[አዳብ]] ንጉሥ ለ[[ሉጋል-አኔ-ሙንዱ]] መንግሥት (2130 ግ.) ግብር ከሚከፍሉ ሕዝቦች መካከል ሲዘረዝሩ ነው። በጽላት መዝገብ ዘንድ አገራቸው ከ[[ሹቡር]] ደቡብና ከ[[ኤላም]] ስሜን ይገኛል። በአካዳውያንም ዘመነ መንግሥት፣ ለንጉሥ [[ታላቁ ሳርጎን]] (2070 ግ.) ተገዥ ሁነው ከ[[ሉሉቢ]] ብሔር አጠገብ ነበሩ። [[ናራም-ሲን (አካድ)|ናራም-ሲን]] (2049-2030 ግ.) ደግሞ የጉቲዩም ንጉሥ ጉላዓን አሸንፎ አገሩን እንደ ያዘው በአንድ ሰነድ ይዘገባል።
 
በ2021 ዓክልበ. ግ. የአካድ ምጉሥ [[ሻርካሊሻሪ]] የጉቲዩምን ንጉሥ ሻርላግን[[ሻርላግ]]ን ማረከው፤ በ2018 ግ. «ቀንበር (ግብር) በጉቲዩም አደረገበት» ይዘገባል። የአካድ መንግሥት ግን ከዚያ ድካም ለመሆን ሲጀምር፣ ጉታውያን በመስጴጦምያ ላይ ብዝበዛ ያድርጉ ነበር። ሠራዊት እንደ ደረሰባቸው ግን ሸሽተው ነበር። ከቤት ማለፍ ወይም እንኳን በእርሻ መግባት አስጊ ሁኔታ ስለ ሆነ፣ የመስጴጦምያ ምጣኔ ሀብት ተበላሸና ራብ ሆነ። በመጨረሻ፣ (2010 ግ.) ጉታውያን አካድን ወረሩና ገዙት። እንዲሁም የጉቲ ሠራዊት [[ኡሩክ]]ንና ኤላምን የዛኔ ወረሩ። የጉታውያን ንጉሥ [[ኤሪዱፒዚር]] እራሱን እንደ አካድ ነገስታት በማምሰል፣ ማዕረጉ 'የጉቲ ንጉሥና የ4 ሩቦች ንጉሥ' ተባለ። ጉታውያን በአገሩ ሁሉ የታሰሩት እንስሶች ከጉረኖአቸው ፈቱ። የጉታውያን ግዛት ለ[[እርሻ ተግባር]]ም ሆነ ለዜና መዋዕል ዝገባ ጥንቁቅ አልነበረም። በ''[[ሱመራዊው ነገሥታት ዝርዝር]]'' በአንዳንድ ቅጂ 25 ዓመታት ብቻ እንደ ገዙ የሚለው አቆጣጠር ትክክል ይመስላል፤ በትንሽ ጊዜ ውስጥ አገሩ በጽኑ ረሃብ ተያዘ። የኤላም ንጉሥ [[ኩቲክ-ኢንሹሺናክ]] ከጉታውያን ዘመን በፊትና በኋላ ስለሚታወቅ ለ124 አመታት (እንደ ሌላ ቅጂ) ሊሆን አይችልም።
 
በ1985 ዓክልበ. ያሕል፣ የኡሩክ ንጉሥ [[ኡቱ-ኸጛል]] የጉታውያን ንጉሥ [[ቲሪጋን]]ን እንዳሸነፈ ጉታውያንንም ከአገራቸው እንዳስወጣ ይባላል። ከዚህ በኋላ በ1974 ዓክልበ. የ[[ኡር]] [[ኡር-ናሙ]] ጉቲዩምን ዘረፈው። በ1676፣ 1674ና 1669 ዓክልበ. የ[[ባቢሎን]] ንጉሥ ሃሙራቢ ጉቲዩምን እንደገና ድል አደረገው።