ከ«ምድያም» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
No edit summary
መስመር፡ 8፦
የእስራኤል ነገዶች ወደ [[ከነዓን (ጥንታዊ አገር)|ከነዓን]] ተምረው በቀረቡበት ጊዜ ምድያም የ[[ሞአብ]] ጎረቤትና ባለሟል ነበር፤ አንድላይ በእስራኤል ላይ ተመካከሩ (ዘኊልቊ ፳፪፡፬-፯)። የሞአብና የምድያም ሴቶች የእስራኤላውያን ወንዶች በማዳራት ወደ [[አረመኔ]] ጣኦታቸው እንዲሰግዱ ያባባሏቸው ጀመር። በዚህ ወቅት የምድያም አለቃ [[ሱር]] ነበር፤ የራሱም ሴት ልጅ [[ከስቢ]]ና የእስራኤል ሰው [[ዘንበሪ]] አንድላይ በድንኳኑ በ[[ፊንሐስ]] ጦር በሆዳቸው ተገደሉ። ምድያም የእስራኤልን ልጆች በዚህ አይነት ሽንግላ ስላስጨነቃቸው [[እግዚአብሔር]] ምድያምን እንዲያጥፉት አዘዘ (ዘኊልቊ ፳፭)። ይህ ዘመቻ በምዕራፍ ፴፩ የገለጻል፤ ሱር እና አራት ሌሎች የምድያም አለቆች (ኤዊ፣ ሮቆም፣ ሑር እና ሪባ) በሠይፍ ተገደሉ። ከ፴፪ ሺህ ድንግል ሴቶች በቀር ወገናቸው ሁሉ ተገደለ፣ የተማረኩት ድንግል ሴቶች ለእስራኤላውያን ተጨመሩ።
 
ሆኖም የምድያም ሕዝብ ሁሉ ያንጊዜ እንደ ጠፉ አይመስልም። በ[[መጽሐፈ መሳፍንት]] ፮፣ ፯፣ ፰ ዘንድ፣ እስራኤላውያን ለ፯ አመታት ለምድያም ተገዙ። የምድያምና የ[[አማሌክአማሌቅ]] ሰዎች ስብሉንሰብሉን ሁሉ ይቀሙ ነበር። [[ጌዴዎን]] ግን አሸነፋቸው፣ የምድያም መኳንንት [[ሔሬብና ዜብ]] ተገደሉ። ከዚያ ጌዴዎን የምድያምን ነገሥታት [[ዛብሄልና ስልማና]] እስከ [[ቀርቀር]] ድረስ አሳደዳቸውና ገደላቸው።
 
በተጨማሪ በ1 ነገሥታት 11:17-18 ዘንድ [[የኤዶምያስ ሰው ሃዳድ]] ከ[[ኤዶምያስ]] ወደ [[ግብጽ]] በሸሸበት ወቅት፣ በምድያምና በ[[ፋራን]] አገሮች እንዳለፈ ይነግራል።