ከ«ርብቃ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
No edit summary
መስመር፡ 4፦
ምዕራፍ ፳፬ እንደሚተርክ፣ አብርሃም ሽማግሌ ሆኖ ልጁም ይስሐቅ የ[[ከነዓን (ጥንታዊ አገር)|ከነዓን]] ሴት እንዳያገባ ከዘመዶቹ ሚስት ያገኝለት ዘንድ ሎሌውን ወደ «[[መስጴጦምያ]]» (ዕብራይስጥ፦ [[አራም-ናሓራይን]]) ላከው። ሎሌው ግመሎችን ይዞ ወደ አብርሃም ወንድም ናኮር ከተማ ደረሰ። ናኮር የኖረው በ[[አራም (ጥንታዊ አገር)|አራም]] አገር ቢሆን ትውልዱ እንደ ወንድሙ አብርሃም ከ[[አርፋክስድ]] ዘር ነበር። የሎሌው ስም ባይሰጥም በ፩ ጥንታዊ ልማድ በምዕራፍ ፲፭፡፪ የተጠቀሰው ሎሌ የ[[ደማስቆ]] ሰው [[ኤሊዔዘር]] ነበረ።
 
ሎሌው ግመሎቹን በውኃ ምንጭ አጠገብ አስቀመጣቸውና ግመሎቼን ያጠጣችው እርስዋ የጌታዬ እጮኛ ትሁን የሚል ጸሎት ጸለየ። ወዲያው ርብቃ መጥትታመጥታ ግመሎቹን አጠጣች። ሎሌው የወርቅ ቀለበትና አምባር ሰጣት። ነገሩን ለቤተሠብዋ ከገለጸላቸው በኋላ፣ አባቷ ባቱኤልና ወንድሟ [[ላባ]] ፈቃዳቸውን ሰጡ። ርብቃና ሎሌው አብረው ወደ ከነዓን በግመል ተመልሰው እርስዋና ይስሐቅ ተያይተው ተዋደዱና ተዳሩ።
 
በምዕራፍ ፳፭ ርብቃ ለይስሐቅ መንታ ልጆች እነርሱም ያዕቆብንና ኤሳውን እንደ ወለደችለት ይነግራል። በምዕራፍ ፳፮ ዘንድ ይስሐቅ በ[[ጌራር]] ቆይቶ ንጉሣቸውን [[አቢሜሌክ]] ርብቃ እህቴ ነች አላት። (በዘፍጥረት ፳ ስለ አቢሜሌክ፣ አብርሃምና [[ሣራ]] ተመሳሳይ ታሪክ አለ፣ በ[[መጽሐፈ ኩፋሌ]] ግን አቢሜሌክ ከይስሐቅና ርብቃ ጋር የነበረው መዋዋል ብቻ ይጠቀሳል፤ እንዲሁም አብርሃምና ሣራ ከ[[ግብጽ]] ፈርዖን ጋር ተመሳሳይ ጉዳይ ነበራቸው።) በኋላ በዘፍጥረት ፳፯ ርብቃ ልጇን ያዕቆብ የኤሳውን በረከት ከይስሐቅ እንዲቀበል መከረችው።