ከ«እስልምና» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
የ41.223.84.35ን ለውጦች ወደ 65.93.200.78 እትም መለሰ።
መስመር፡ 6፦
:2ኛ እርቅ እና እርጋታ
:3ኛ ሰሚነት እና ቅን ታዛዥነት የሚለውን ትርጉም አዝሎ ይገኛል።
=== የ''ኢስላም'' ህጋዊ ትርጉም ===
''ኢስላም'' ማለት ለፈጣሪ እጅን መስጠት እና በትእዛዙ ማደር (ስብሚሽን ቱ ዘ ዊል ኦፍ ጎድ) ማለት ሲሆን አምልኮትን ሁሉ በብቸኝነት ፍጹም ለአላህ ማድረግ ። ሌሎችን ፍጡራን የስልጣኑ ተጋሪ አለማድረግ፡ ይህን ዩኒቨረስ ብቻውን የፈጠረ /ለፍጡራን ሁሉ ሲሳያቸውን እሱ ብቻውን የሚመግብ /ለስልጣኑ ተጋሪ ወይም እረዳት ተባባሪ የሌለው ሃያል ጌታ መሆኑን ማመን። ነገ የትንሳኤ ቀን የፍርዱ ቀን ብቸኛ ባለቤት አላህ መሆኑን ማመን። ይህን ይመስላል ብለን የምንመስልበት አምሳያ የሌለው ሃያል አምላክ አላህ በመባል ይታወቃል።
 
ኢስላም ማለት ለአላህ በመመሪያው በማደር ለትእዛዞቹ መንበርከክ ፡ እምነትን እና ልቦናን ለአላህ ፍጹም ማድረግ እና ከአላህ ዘንድ የመጡ መመሪያዎችን በፍጹምነት ማመን ነው።
 
* አንድ ሰው ''ሙስሊም'' ነው ሊባል የሚቻለው የዚህ ግዙፍ አለም ሆነ ሌላ አለ የሚባለው አለም እና በውስጧ ያሉት ነገሮች ሁሉ ፈጣሪ ተቆጣጣሪ አስተናባሪ ብቸኛ አምላክ አላህ ነው ብሎ ማመን እና ነቢዩ ሙሃመድ የመጨረሻው መልእክተኛ ናቸው ብሎ ማመን ነው። ይህም በሌላ አነጋገር በእውነት የሚያመልኩት አምላክ ከአላህ በስተቀር የለም። ነብዩ ሙሐመድም(ሰላም ለእሳቸው ይሁንና) ባሪያው እና መላክተኛው ናቸው ብሎ ማመን ነው። ይህም በ[[አረብኛ]] «''ላኢላሃ-ኢለሏህ ሙሃመድ ረሱሉሏህ''» በመባል ይታወቃል።
 
በዓለም ላይ የእምነቱ ተከታዮቹ ከ1.፮ ቢሊዮን በላይ ሆነው ይገኛሉ።
 
ሱና ማለት የነብዩ ሙሐመድ ንግግር እና ስራ/ስሩ ብለው ያዘዙት እና ሲሰራ እያዩ በዝምታያለፉት (አትስሩ ብለው ያልከለከሉት) በአጠቃላይ በህይወታቸው የሰሩት ስራ እና እንዲሰራ ያዘዙት ሁሉ ሱና ይባላል።
 
Line 55 ⟶ 64:
4ኛ በሩሱሎች ማመን ማለት አላህ ይህን ዓለም ከፈጠረ ጀምሮ እስከ ነብዩ ሙሐመድ ድረስ ሰዎች ቀጥተኛውን የኢስላም መንገድ ይዘው ይጓዙ ዘንድ ነብያትን መረክተኛ ድርጎ ልኳል ።ስለዚህ በሩሱሎች (ማለት መላክተኛ ማለት ነው)በመላካቸው ማመን
 
5ኛ በመጨረሻው ቀን ማመን ማለት ይህ አለም መጨረሻ እንዳለው እና በዚህ ምድር የሰራውን ስራ ተገምግሞ እና ታስቦ መልካም ሰሪው በጀነት የሚመነዳበት በጥፎ ሰሪው በገሃነም የሚቀጣበት የሂሳብ እርና የፍርድ ቀን አለ ብሎ ማመን ማለት ነው።
5ኛ1ኛ አላህ አንድ ነው ሙ
 
ይህ የፍርድ ቀን የትንሳኤ ቀን ማለት ሲሆን ልክ ከ እንቅልፋችን እንደምንነሳው ሁሉ ሁሉም ሰው ከመቃብሩ እየተነሳ ወደ ፍርዱ ቀን ሜዳ የሚሰበሰብበት ቀን መኖሩን ማመን።
 
 
6ኛ በቀዷ በቀደር ማመን ማለት። ጥሩም ይሆን መጥፎ ነገር ተጽፎ እና ተወስኖ ያለፈ መሆኑን አምኖ በጸጋ መቀበል ማለት ነው። አንድ ሰው ወደዚህ ምድር ከመምጣቱ በፊት በምድራዊ ህይወቱ ምን እንደሚያጋጥመው ተወስኖ ተጽፎ አልፏል። ስለዚህ ያልተጻፈበትር አያገኘውም ያልተጻፈለትንም አያገኝም።
እሱ ግን እጣ ፈንታው ምን እንደሆነ ስለማያያውቅ ፈጣሪ ያዘዘውን ብቻ ትእዛዝ መፈጸም ነው ያለበት። አላህ የምንፈልገውን እንድንሰራ ጫና ሳያደርግ ምርጫ ሰጥቶናል።
የኢስላም መሰረቶች በ 5 ይከፈላሉ ብለናል
 
1ኛ አላህ አንድ ነው ሙሐመድ መላክተኛ ነው ብሎ ማመን ማለት ነው። ይህ የእምነቱ የማዕዘን ድንጋይ ወይም ቁልፍ ነው ማለት ይቻላል። አንድን ሙስሊም ሙስሊም ያሰኘው እና ከሙስሊሞች ቤተሰብ እንዲቀላቀል የሚያደርገው ወሳኝ ቃል በአረብኛ ላኢላሃ ኢለሏህ ሙሐመድ ረሱሉሏህ የሚባለው በአማርኛ ደግሞ በ እውነት የሚያመልኩት ጌታ ከላህ በስተቀር የለም የሚለው ቃል ነው።
 
2ኛው ሰላት መስገድ ሲሆን የትንሳኤ ቀን ለመጀምሪያ ጊዜ የሰው ልጅ ሂሳቡ የሚጀምረው ከሰላት ነው፡፡ ሰላቱ የጎደለ ሰው ሌኤላው ስራው አይሞላለትም። ለዚህም ነው ሙስሊም ብነሆነው እና ባልሆነው ሰው መካከል ያለው ልዩነት ሰላት መስገድ ነው በማለት ነብዩ ሙሀመድ ያስተማሩት።
ሰላት በቀን 5 ጊዜኤ ሰአት ተወስኖለት የሚተገበር የአምልኮት አይነት ሲሆን እነሱም ፈጅር (ሱብህ) ዝሁር አስር መግሪብ ኢሻ በመባል ይታወቃሉ። እነዚህ በማንኛውም አካለመተን በደረሰ እና ዐምሮው ጤነኛ በሆነ ሙስሊም ላይ የግዴታ ሰላቶች ናቸው። ሌሎች ደግሞ ዱሃ እና የሌሊት ሰላት የሚባሉ በፈቃደኝነት ላይ የተመሰረቱ ታላቅ ምንዳ የሚያስገኙ የሰላት አይነቶች አሉ።
የፈጅር ሰላት ሁለት ረከዓ ሲሆን የሚሰገደው ከፈርድ ሰላት በፊት(ከዋናው የፈጅር ሰላት በፊት 2 ረከዓ ሱና ይሰገዳል። የፈጅርን ሰላት መስጊድ ውስጥ ከህዝቡ ጋር በጋራ (ጀመአ) የሰገደ በአላህ ጥበቃ ስር እንደሚውል ነብዩ ተናግረዋል።
 
** ዝሁር ሰላት 4 ረከአ ሲሆን ከዋናው ሰላት በፊት እና በኋላ ሁለት ሁለት ወይም አራት አራት ረከአ ሱና መስገድ ይወደዳል። አስር 4 ረከአ ሲሆን ከዋናው ሰላት በፊት ሁለት ሁለት እያደረጉ 4 ረከአ ሱና መስገድ ይወደዳል። መግሪብ 3 ረከ ሲሆን ኢሻ 4 ረከአ ሰላት ነው።
ከኢሻ በፊት እና በኋላ ሱና ቢሰገድ ይወደዳል።
 
አንድ ሙስሊም ሰላት አይጠቅምም አያስፈልግም ብሎ ከተውው ከ ኢስላም ጓዙን ጠቅልሎ ይወጣል።
 
በስንፍና እና በ እንዝህላልነት አንዴ እየስገደ አንዳንዴ የሚተወው ከሆነ ደግሞ በጣም ከባድ ማስጠንቀቂያ እና በቁር አን ወዮለት የሚል ዛቻ ስላለ አንድ ሙስሊም ሙስሊም ሊባል የሚችለው ሰላትን በወቅቱ እና ደንቡን ጠብቆ ሲሰግድ ብቻ መሆኑ ሊሰመርበት ይገባል።
 
በጅመዓ (መስጊድ ከህብረተሱ ጋር) ሆኖ መስገድ ብቻን ከመስገድ በ27 ደረጃ ይበልጣል። ስለዚህ አንድ ሙስሊም የአዛን ጥሪ መስማት ከቻለመስጊድ ሄዶ የመስገድ ግዴኤታ አለበት
ለዚህም ነው ሰላትን የተወ ሰው በ እስልምና ምንም ነሲብ(እድል ) የለውም የሚባለው፡
ነብዩ ሰለላሁ አለይሂ ወሰልም ሰላት የአይናቸው ማረፊያ እና የልባቸው መርጋጊያ ነበረች። አንድ ሰው ወደ አላህ ከሚቃረብበት አንዱ ሶላት ነው።
 
3ኛ ዘካን ማውጣት። ወይም ምጽዋት የመስጠት ግዴታ ነው። ምጽዋት መስጠት ማለት አንድ ሰው ከቀለቡ እና ከልብሱ ከተለያየ ወጭ ተርፎት 10 ሽ ብር ለአንድ አመት ያክል ካስቀመጠ 2.5% ማለት 250 ብር ዘካ (ምጽዋት የመስጠት ግዴኤታ አለበት) ዘካ በትክክል ቢወጣ ኖሮ በአለም ላይ ደሃ የሚባል አይገንም ነበር።
 
ስለዚህ ዘካ (ምጽዋት መስጠት በ እስልምና ግዴታ ነው።) ይህም ለአንድ አመት ተቀማጭ ገንዘብ ካለው ነው ይህ ገንዘብም የ85 ግራም ወርቅ መጠን ሲደርስ ነው።
4ኛ የረመዳን ጾም በማንኛውም ሙስሊም ላይ ግዴታ ነው። በሽተኛ ካልሆነ ዐምሮውን የሳተ እብድ ካልሆነ እና ሴቶች በወር አበባ ጊዜኤ ካልሆኑ እንዲሁም መንገደኛ ካልሆኑ በስተቀር በአረበኛ የቀን አቆጣጠር 9ኛ ወር ላይ የሚገኘውን 1 ወር ረመዳን ሙስሊሞች የመጾም ግዴታ አለባቸው። ጾም ብዙ ጥቅሞች አሉት ። ሰዎች ረሃብ መኖሩን ሲያውቁ ነው ለተራበ የሚያዝኑት። በረመዳን ጾም ጊዜኤ ሰደቃ (ምጽዋት መስጠት) በጣም ይወደዳል።
 
 
 
ጾም ማለት ጎህ ከመቅደዱ በፊት ጀምሮ ጸሃይ እስክትጠልቅ ከምግብ እና ከመጠጥ እንዲሁም ከግብረ ስጋ ግንኙነት ራስን ማቀብ ማለት ሲሆን ምላስንም ከዛዛታ ወሬ እና ከውሸት ከሃሜት መቆጠብ የግድ ይሆናል። ምግብ እና መጠጥ መተው ብቻ ጾም ጾም አያደርገውም።
ነብዩ ሙሐመድ በሃዲሳቸው ላይ በውሸት መናገር እና መስራት ያላቆመ ሰው ምግብ እና መጠጥ ማቆሙ ብቻ ዋጋ እንደሌለው ተናግረዋል። ስለዚህ ምላስም ከመጥፎ ንግግር ከሃሜት ከውሸት መጾም አለበት። አይንም መትፊ ነገር ከማየት ጆሮም መጥፎ ነገር እና ዛዛታ ወሬ ሙዚቃ ከመስማት መታቀብ አለበት።
 
5ኛው ሃጅ ማድረግ ሲሆን ይህም ለቻለ ሰው ብቻ ነው። ይህም ማለት የሃጅን ስነ ሥር ዓት ለማሟላት መካ አድርሶ የሚያመጣው ገንዘብ ያለው ሰው እና እሱ ደርሶ እስኪመጣ ቤተሰቦቹ እንዳይቸግራቸው ለነሱ የሚተውላቸው ትርፍ ገንዘብ ባለው ሰው ላይ ሃጅ በሂወቱ አንዴኤ ግዴኤታ ይሆናል። ይህን እየቻለ ሃጅ ሳያደርግ ከሞተ ከተጠያቂነት አያመልጥም።
 
የሃጅ ስነ ስር አት ስብስብ ሁሉም ነገ የትንሳኤ ቀን አላህ ፊት የሚሰበሰብበትን ሁኔኤታ የሚያስታውስ ከ4 ሚሊዮን በላይ ህዝብ በየአመቱ የሚሰበሰብበት ታላቅ ኢስላማዊ ስብስብ ነው። ሃጅ አደረገ እንዲባል እና ሃጅ እከሌእ እንዲሉኝ ብሎ ሳይሆን ከዛዛታ ወሬኤ ከአጉል ሰባይ እና ተግባር ተቆጥቦ ሃጅ ያደረገ ሰው እናቱ እንደወለደችው ሕጻን ሆኖ ወንጀሉ ይማርለታል። እንግዲህሃዲስ የተወለድ ህጻን ምንም አይነት ወንጀል የለበትም ማለት ነው። ይህ ግን የሰውን ገንዘብ የበላን አይጨምርም የሰው ገንዘብ የወሰደ ለባለቤቱ እስካልመለሰ ድረስ በኢስላም ይቅርታ አይደረግለትም። ምክንያቱም የግለሰብ መብት ስለሆነ በዚህ ምድር እንኳ ሳይከፍል ቢሞት የትንሳኤ ቀን ከመልካም ስራው የከፍላል። መልካም ስራ ከሌለው ገንዘብ የበላበትን ሰው ወንጀል ይሸከማል።
 
ሃጅ ሁለት ፎጣ የሚእስሉ ነጭ ልብሶችን ለወንዶች ካለ ውስጥ ሱሪ የሚለበስበት እና ሁሉም ሰ እራቁትን እንደተፈጠረ እራቁቱን ወደሚቀጥለው አለም እንደሚሄድ የሚያስገነዝቡ ነገሮ/በሃጅ ቦታ ሃብታሙ ከደሃው ዶክተሩ ከገበረው የማይለይበት ሁሉም ወንድ ነጭ ልብስ ለብሶ በአረፋ ላይ የሚሰበሰብበት ሁኔኤታ አለ። አንድ ሰው የሃጅን ግዴታ ተወጣ የሚባለው አረፋ ላይ መዋል ሲችል ነው። ሴቶች የሰውነታቸውን ቅርጽ የማያሳይ ማንኛውም አይነት ልብስ መልበስ ይፈቀድላቸዋል።'''Bold text'''
 
ስድስቱ የእስልምና ሃይማኖት መግለጫዎች
እነዚህ ትምህርቶች የእስልምና መሠረታዊ እምነቶች ናቸው፡፡ ማንኛውም ሙስሊም እውነተኛ ሙስሊም ለመባል እነዚህን መሠረታዊ የእምነት አቋማት ሊከተላቸውና ሊፈጽማቸው ይገባል፡- (1) በአንድ ፈጣሪ ማመን (2) በሁሉም የፈጣሪ ነቢያት ማመን (3) ከአላህ ዘንድ ለነቢዩ ሙሴ፣ ለዳዊት፣ ለኢየሱስ እና ለሙሐመድ በተገለጡትን ቀደምት የቅዱሳት መጻሕፍት ቅጂዎች ማመን (4) በመላእክት ማመን (5) ስለ ፍርድ ቀን እና ከዛ በኋላ ስላለው ሕይወት ማመን (6) በመለኮታዊ አዋጅ (ወይም የፍጻሜ እጣ ፈንታ) ማመን፡፡ ለተጨማሪ መረጃ የሚከተለውን ሊንክ ይጫኑ http://islam-in-ethiopia.blogspot.com
በ አጠቃላይ ኢስላም ከ አለም ላይ ካልሉት ሃይማኖቶች አንደኛ ነው።
{{Link FA|ar}}
{{Link FA|ceb}}
{{Link FA|eo}}
{{Link FA|hu}}
{{Link FA|id}}
{{Link FA|ms}}
{{Link FA|tr}}
{{Link GA|es}}
{{Link GA|zh}}