ከ«ዝግመተ ለውጥ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
ሎሌ፦ መያያዣዎች ወደ 105 ልሳናት አሁን በWikidata ገጽ d:q1063 ስላሉ ተዛውረዋል።
Robot: Removing selflinks
መስመር፡ 3፦
የአንድ ሕይዎት ያለው ማህብረሰብ የዘር ውርስ ባህሪይ ከትውልድ ወደትውልድ እየተቀየረ መሄዱ '''ዝግመተ ለውጥ''' ይባላል። [[ቻርለስ ዳርዊን]] ይህን ኩነት በማስተዋልና በሳይንሳዊ [[አመክንዮ]] አሰደግፎ በመተንተኑ የመጀመሪያው ሰው ነው። ዳርዊን በተጨማሪ [[የተፈጥሮ ምርጫ]] ባለው [[ኅልዮት|ኅልዮቱ]] ሕይዎት ያላቸው ማህበረሰቦች ዝግመተ ለውጥ እሚያካሂዱት ምንም እንኳ በዘፈቀደ ስህተት እየፈጸሙ ቢሆንም፣ ተፈጥሮ እራሷ በምትፈጥረው መሰናክሎች እኒህን መሰናክሎች አልፈው የሚሄዱትን በመምረጧ ነው። ዳርዊን የተፈጥሮ ምርጫን አስተሳሰብ ከ፫ የሚታዩ ነገሮች አንጥሮ ነበር ያወጣው፦ ፩) እንስሳትም ሆነ እጽዋት ወደፊት ሊኖር ከሚችሉ ዘሮች በላይ አተረፍርፈው ነው እሚራቡት ፪)ሕይወት ያላቸው እያንዳንዳቸው ነገሮች ሁልጊዜ የተለያየ ጸባይ ነው ያላቸው፣ ስለሆነም እያንዳንዳንቸው በቀጣይ የመኖር ዕድላቸው የተለያየ ነው ፫) ስለሆነም የአንድ ማህበረሰብ አባላት ሲሞቱ፣ የሚገላቸውን ነገር ጠንክረው እሚቋቋሙት ግለሰቦች ብቻ በሕይዎት ቆይተው ወደፊት መራባች ይችላሉ። ስለሆነም ቀስ በቀስ እነዚህ በህይዎት ያሉ፣ በህይዎት የሌሉትን አይነቶች እየተኩ ይሄዳሉ።
 
በ፳ኛው ክፍለ ዘመን [[ጄኔቲክስ]] እና [[ዝግመተ ለውጥ]] ተዋህደው [[ማህበረሰባዊ ጄኔትክስ]] እሚባለውን ጥናት ለመፍጠር ችለዋል። አንድ ማህበርሰብ ለየት ያለ ግለሰቦችን ለመፍጠር ከሚያስችሉት መንገዶች አንዱ [[ሙቴሽን]] የተባለው ሂደት ሲሆን፣ ሙቴሽን እሚፈጠረው የዚያ ግለሰብ [[ዲ ኤን ኤ]] ከወላጆች ሲዎረስ በሚደረግ ስህተት ነው።
 
{{መዋቅር}}