ከ«ታራ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
ሎሌ፦ መያያዣዎች ወደ 28 ልሳናት አሁን በWikidata ገጽ d:q586541 ስላሉ ተዛውረዋል።
Robot-assisted disambiguation: ከነዓን - Changed link(s) to ከነዓን (ጥንታዊ አገር)
መስመር፡ 2፦
'''ታራ''' ([[ዕብራይስጥ]]፦ תָּרַח /ታረሕ/) በ''[[ኦሪት ዘፍጥረት]]'' መሠረት የ[[ናኮር]] ልጅና የአብራም ([[አብርሐም]]) አባት ነበረ።
 
''ዘፍጥረት'' 11፡26-32 ስለ ታራ በ[[አማርኛ]] እንደሚለው፣ የታራ ዕድሜ 100 ዓመት ሲሆን አብራም፣ [[2 ናኮር]]ና [[ሐራን]] የተባሉትን ወንድ ልጆች ወለደ። ከዚያ በኋላ ሐራን የ[[ሎጥ]] አባት ሆነ፣ ዳሩ ግን ታራና ቤተሠቡ በ[[ከለዳውያን ዑር]] ገና እየኖሩ ልጁ ሐራን ሞተ። አብራም ሚስቱን ሦራን ([[ሣራ]]ን) አግብቶ እስዋ ግን መካን ነበረች። ከግዜ በኋላ ታራ ልጁን አብራምን፣ የአብራምንም ሚስት ሦራንና የልጁን ልጅ ሎጥን ወሰዳቸው፣ ከከለዳውያን ዑር ወደ [[ከነዓን (ጥንታዊ አገር)|ከነዓን]] አገር ለመዛወር ተጓዙ። ሆኖም [[ካራን]] የሚባለውን ከተማ በደረሱ ጊዜ መንገዳቸውን ተዉና በዚያ ተቀመጡ። በጠቅላላ የታራ ዕድሜ 205 ዓመታት ነበረ። (በ[[ዕብራይስጥ]]፣ [[ግሪክ (ቋንቋ)|ግሪክ]]ና በ[[ሳምራዊው ትርጉም|ሳምራዊው]] ትርጉሞች ዘንድ፣ ታራ ልጆቹን ሲወልድ እድሜው 70 አመት ብቻ ነበረ። በተጨማሪ፣ በሳምራዊው ትርጉም ዘንድ የታራ እድሜ በጠቅላላ 145 ዓመታት ብቻ ደረሰ።)
 
በ''[[መጽሐፈ ኩፋሌ]]'' 10፡28-11፡16 ዘንድ፣ ታራ ከአባቱ ናኮርና ከእናቱ ኢዮስካ በ1806 አመተ አለም ተወለደ። በዚያን ጊዜ ክፉ አዕዋፍና በተለይ [[ቁራ]]ዎች የሰው ልጅ የዘራውን የአትክልት ዘር ከከላውዴዎን እርሻዎች ይበሉ ነበር። በ1870 አ.አ. ታራ ሚስቱን [[ኤድና]]ን አገባት፤ እርሷም የ[[ሴሮሕ]] ልጅ አብራም ልጅ ነበረች። በ1876 አ.አ. ኤድና ልጁን አብራምን ወለደችለት፤ ስለዚህ የታራ እድሜ 70 ዓመታት ነበረ። የታራ ቤተሠብ እንደ ሰው ልጅ ሁሉ ጣኦታትን ያመለኩ አረመኔዎች ነበሩ፤ ታራም እራሱ የጣኦታት መቅደስ ቄስ ነበረ። አብራም ግን በወጣትነቱ ከአባቱ ታራ እምነት መለየት ጀመረ፣ የአብራምም እድሜ 15 አመታት ሲሆን አዕዋፍን ለመከላከል [[ማረሻ]]ን ፈጠረ፤ ስመ ጥሩ ሆነ። በ1903 አ.አ. ግን አብራም አባቱን ስለ ጣኦታት እንዳያመልካቸው፤ ሕያው [[እግዚአብሔር]]ን ብቻ እንዲያመልክ ለመነው። ታራም እውነትህ ነው፣ ግን የጣኦታት መቅደስ ቄስ ሆኔ እውነቱን ብነግራቸው ሕዝቡ ይገድሉናል እንዳይገድሉህ አንተም ዝም በል ብሎ መለሰው። በ1936 አ.አ. ግን አብራም መቅደሱን ጣኦታቱንም በሙሉ አቃጠላቸው። ወንድሙም ሐራን ጣኦታቱን ለመጠብቅ ሲያስብ በዚሁ እሳት ሞተ። ስለዚሁ ድርጊት ታራና ቤተሠቡ ወደ ከነዓን አገር ለመሸሽ ተጓዙ፤ ሆኖም በካራን ከተማ ደርሰው ተቀመጡ። በ1953 አ.አ. በካራን ሲቀመጡ ታራ ልጁን አብራም፣ የአብራምም ሚስት ሦራንና የልጁን ልጅ ሎጥን ወደ ከነዓን አገር አሰናበታቸው።
ከ «https://am.wikipedia.org/wiki/ታራ» የተወሰደ