ከ«ጳውሎስ ኞኞ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
Robot-assisted disambiguation: አዲስ ዘመን - Changed link(s) to አዲስ ዘመን (ጋዜጣ)
መስመር፡ 1፦
[[ስዕል:Paulos gnogno.jpg|300px|thumbnail|right|ጳውሎስ ኞኞ (በስተግራ)]]
[[Image:Paulos_GnoGno.jpg|thumb|180px|አቶ ጳውሎስ ኞኞ]]
ደራሲ '''ጳውሎስ ኞኞ''' [[ኅዳር 11]] ቀን [[1926]] ዓ.ም [[ቁልቢ]] አካባቢ ተወለደው [[ድሬዳዋ]] ከተማ አደጉ። በ[[ጣሊያን]] ወረራ ምክንያት ትምህርታቸውን ከ4ኛ ክፍል በላይ ለመቀጠል አልቻሉም ነበር። ብልህ አዕምሮና የፈጠራ ችሎታ የነበራቸው ሰው ስለነበሩ፤ በልጅነታችው የ[[ኢትዮጵያ]] ጀግኖች [[አርበኞች]] ጣሊያንን ሲገድሉ ወይንም ሲማርኩ [[ሥዕል]] በመሣል ያሳዩ ነበር። ጳውሎስ ካላቸው የጽሑፍ ጥማት የተነሳ የ«ድምጽ ጋዜጣ» አዘጋጅ በመሆን የብዕር ድምጻቸውን ያሰሙ ነበር። ጋዜጦች ላይ ከጽሑፍ አቅራቢነት እስከ አዘጋጅነት ለበርካታ ዓመታት ሠርተዋል። በተለይ «አንድ ጥያቄ አለኝ» በሚለው የ[[አዲስ ዘመን (ጋዜጣ)|አዲስ ዘመን]] ጋዜጣ አምዳቸው ላይ ብዙ ታዋቂነትን አግኝተዋል። አቶ ጳውሎስ ኞኞ ከ[[1955]] ዓ.ም ጀምሮ ለኢትዮጵያ [[ስነ ጽሑፍ]] ዕድገት የነበራቸውን ተሰጥኦ በአግባቡ በሥራ ላይ ያዋሉ እውቅ ጋዜጠኛና ደራሲ ነበሩ።<ref>''ብሔራዊ ቢብሎግራፊ'' (የደራሲያን አጭር የሕይወት ታሪክ) ፲፱፻፺፰ ዓ.ም. [http://www.nale.gov.et/National%20Bibliography/BIBLIO.%20OF%20ETHIOPIAN%20WRITERS%20.pdf]</ref> እኚህ ታዋቂ ሰው በተወለዱ በ58 ዓመታቸው ሞቱ።
 
አቶ ጳውሎስ ''የጌታችው ሚስቶች'' በሚል ርዕስ ያሳተሟትን መጽሐፍ፤ «ከታተመችበት ወር አንሥቶ ላንድ ዓመት የመጽሐፌ መብት የግሌ ነው፡ ከአንድ ዓመት በኋል መብቱ የማንኛውም ኢትዮጵያዊ ይሁን፡ ከወሰንኩት ጊዜ በኋላ አሳትሞ ለመሸጥ የፈለገ ሁሉ ከድርሰቴ ሳይቀንስም ሆነ ሳይጨምር ሊያራባው ይችላል። ስሜን ሳይሰርዝ 'አሳታሚውን እገሌ' ብሎ ማንም ኢትዮጵያዊ ከፈለገ እንዲያራባት የደራሲነት መብቴን ልቅቄአለሁ፡ አሳታሚው የግሉን የመግቢያ ሐተታ በስሙ ቢጽፍ እኔም ሆንኩ ወራሼ አንቃወምም።» ብለዋል