ከ«ገንዘብ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
ሎሌ፦ መያያዣዎች ወደ 132 ልሳናት አሁን በWikidata ገጽ d:q1368 ስላሉ ተዛውረዋል።
Robot-assisted disambiguation: ብር - Changed link(s) to የኢትዮጵያ ብር, ብር (ብረታብረት)
መስመር፡ 1፦
[[ስዕል:Euromoenterogsedler.jpg|thumb|right|[[ሳንቲም]] እና [[የኢትዮጵያ ብር|ብር]] – በብዛት በስራ ላይ በተጨባጩ አለም ውስጥ የተሰማሩ የገንዘብ አይነቶች ናቸው። ገንዘብ ከነዚህ ውጭ ሊሆን ይቻላል።]]
በአንድ አገር ወይም ማህበረሰብ ውስጥ ለ[[ሸቀጥ]] (አሰፈላጊ እቃ) ና [[አገልግሎት]] መግዢያ እንዲሁም [[እዳ]] መክፈያ የሚያገለግ ማንኛውም ነገር ሁሉ '''ገንዘብ''' ይባላል።
 
የጥንቱ ገንዘብ [[ዋጋ]] ይመነጭ የነበረው ከራሱ ከተሰራበት እቃ ዋጋ ነበር (ለምሳሌ፡ ከወርቅ የተሰራ ሳንቲም) ። በዚህ ምክንያት እንዲህ አይነቱ ገንዘብ የ[[ኮሞዲቲ ገንዘብ]] ይባላል። በአሁኑ በአለማችን የሚሰራባቸው ገንዘቦች በራሳቸው የራሳቸው የሆነ ዋጋ የላቸውም (ለምሳሌ ከ[[ተልባ እግር]] የተሰራው ዶላር በራሱ ዋጋ የለውም) ። ይህ አይነት ገንዘብ [[ፊያት ገንዘብ]] ሲባል ዋጋው የሚመነጨው የአንድ አገር መንግስት ህጋዊ መገበባያ ብሎ ስላወጀው ብቻ ነው። ህጋዊ መገበባያ ሲባል ለማንኛውም በዚያ አገር ውስጥ ላለ እዳ ይህ የታወጀው ገንዘብ እንደ ክፍያ ሲቀርብ "አይ! አልቀበልም" ማለት ክልክል ነው። በዚህ ምክንይት የፊያት ገንዘብ ዋጋ ከመንግስት ሃይል ጋር ከፍተኛ ግንኙነት አለው።
 
ያንድ ዘመናዊ ሃገር የ[[ገንዘብ አቅርቦት]] በሁለት ይከፈላል፣ ይኸውም ተጨባጭ የሆነው የታተመው [[የኢትዮጵያ ብር|ብር]]ና በማይጨበጥ መልኩ በ[[ባንክ]] ቤት ተጠራቅሞ ያለው በ[[ቼኪንግ]] እና [[ሴቪንግ]] የሚከፈለው የ[[ባንክ ሒሳብ]] ነው። ባብዛኛው ጊዜ እኒህ የ ባንክ ሒሳቦች ታትሞ ከቀረበው ብር በላይ ናቸው። በምናባዊ አለም ውስጥ የተቀመጡት እነዚህ የቁጥር ሰነዶች ምንም እንኳ የማይታዩና የማይዳሰሱ ቢሆንም ልክ እንደ ጥሬ ብር እኩል ለመሸጥና ለመለወጥ ያገለግላሉ። <ref>{{cite web|url=http://www.philadelphiafed.org/education/money-in-motion/treasure-trove/ |title=Learn More About Coins and Money — Treasure Trove - Philadelphia Fed |publisher=Philadelphia Fed. |date= |accessdate=2009-04-20}}</ref><ref>{{cite web|url=http://www.pbs.org/newshour/on2/money/history.html |title=On2 Money / A History of Money |publisher=Pbs.org |date= |accessdate=2009-04-20}}</ref> <ref>Bernstein, Peter, ''A Primer on Money and Banking, and Gold'', Wiley, 2008 edition, pp29-39</ref>
 
== ታሪክ ==
መስመር፡ 10፦
* የጥንቶቹ ሰወች እቃን በቃ በመለዋወጥ መገበያየት ቻሉ። ይህም በማይተዋወቁ ሰወች ዘንድ ነበር። በሚተዋወቁ ግን የስጦታ ልውውጥ ይደረግ ነበር።<ref>Graeber, David. 'Toward an Anthropological Theory of Value'. pp. 153-154.</ref>
* ቀስ ብሎ የተለያዩ ባህሎች [[ኮሞዲቲ ገንዘብ]] መጠቀም ጀመሩ። በተለይ [[ዛጎል]] በብዙ ህብረተሶቦች ዘንድ እንደ መገበባያ ገንዘብ ይጠቅም ነበር። <ref>Kramer, ''History Begins at Sumer'', pp. 52–55.</ref> እንደ ታሪክ ጸሃፊው [[ሄሮዱተስ]] ለመጀመሪያ ጊዜ የ[[ወርቅ ሳንቲም]] እና የ[[ብር ሳንቲም]] መጠቀም የጀመሩት [[ልድያ|ልድያውያን]] ነበር።.<ref>Herodotus. ''Histories'', I, 94</ref> በኢትዮጵያም በ[[አክሱም]] ነገሥታት የታተሙ የወርቅ ሳንቲሞች ስራ ላይ ውለዋል።
* ከዚህ ቀጥሎ የተነሳው [[ተወካይ ገንዘብ]] የሚባለው ገንዘብ አመጣጡ እንዲህ ነው። [[ወርቅ]]ና [[ብር (ብረታብረት)|ብር]] ነጋዴወች ለደንበኞቻቸው [[ደረሰኝ]] በመጻፍ፣ ያንን ደረሰኝ ደምበኞች በማምጣት በፈለጉት ሰዓት ወርቁንና ብሩን ማግኘት ቻሉ። ቀስ በቀስ ደረሰኙ በወርቁና በብሩ ቦታ ተተክቶ እንደ ሙሉ ገንዘብ መስራት ጀመረ። የወረቀት ገንዘብ ለመጀመሪያ ጊዜ ጥቅም ላይ የዋለው በ[[ሶንግ ስርወ መንግስት]] (970 ዓ.ም. - 1276 ዓ.ም.) ዘመን በ[[ቻይና]] አገር ነበር፣ ብሮቹም [[ያወዚ]] ይባሉ ነበር፣ አመጣጣቸውም ከላይ እንደተገለጸው የ[[ደረሰኝ]] ጽሁፈትን ተከትሎ ነው። [[አውሮጳ]] ውስጥ የወረቀት ገንዘብ ለመጀመሪያ ጊዜ ጥቅም ላይ የዋለው በ1661፣ [[ስዊድን]] አገር ነበር። በዚህ ወቅት እያንዳንዱ ጥሬ የወረቀት ብር ወደ ተወሰነ የወርቅ ክብደት የሚቀየርበት ስሌት ነበረው። በ20ኛው ክፍለ ዘመን መጀሪያ ላይ ይህ በ[[ወርቅ የተደገፈ]] የተሰኘው የገንዘብ ስርዓት በመላው ዓለም ተንሰራፋ።
* ከ[[ሁለተኛው የዓለም ጦርነት]] በኋላ በ[[ብሬቶን ውድስ ስብሰባ]]፣ አብዛኞቹ የአለማችን አገሮች [[ፊያት ገንዘብ]]ን በማጽደቅ ገንዘባቸውን በቀጥታ በወርቅ ከመደገፍ ይልቅ ከ[[አሜሪካን ዶላር]] አንጻር እንዲተረጎም አደረጉ። የአሜሪካን ዶላር በተራው በወርቅ የተደገፈ ነበር።
* በ1971 የአሜሪካን መንግስት ዶላሩን በወርቅ መደገፍ/መተርጎም አቆመ። ከዚህ በኋላ ሌሎቹም አገሮች የየራሳቸውን ገንዘብ ከአሜሪካን ዶላር አንጻር መተርጎም አቆሙ። በአሁኑ ወቅት አብዛኛው የአለማችን ገንዘቦች በወርቅም ሆነ በሌላ ቋሚ ነገር የሚደገፉ ሳይሆን በየአገሩ ባሉ መንግስታ እንደ ህጋዊ መገበባያ በወጡ አዋጆች ምክንያት ነው።