ከ«ጥር ፲፫» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
Robot-assisted disambiguation: እንግሊዝ - Changed link(s) to ዩናይትድ ኪንግደም
መስመር፡ 6፦
*[[1864|፲፰፻፷፬]] ዓ.ም.፣ ደጃዝማች ካሳ ምርጫ (አባ በዝብዝ) በ[[አክሱም ጽዮን ማርያም]] ቤተ ክርስቲያን ስመ መንግሥታቸው "ዮሐንስ ራብዓዊ" ([[ዮሐንስ ፬ኛ]]) ተብሎ፣ በጳጳሱ በብፁዕ አቡነ አትናቴዎስ እጅ ተቀብተው በሥርዓተ መንግሥት ንጉሠ ጽዮን፣ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ ተብለው ነገሡ። በታሪክ እንደተመዘገበው በዚሁ ንግሥ ምክንያት ሦስት ቀን በዓል ሆኖ፣ ለግብር ፬ ሺህ ሰንጋ ታርዶ፣ ፶ ጉንዶ ማር የፈጀ፣ ፻፶ ሺህ ገንቦ ጠጅ ቀርቦ፣ በደስታ ሲበላ ሲጠጣ ሰንብቷል።
 
*[[1933|፲፱፻፴፫]] ዓ/ም የ[[ፋሺስት ኢጣሊያ]]ን ሠራዊት ጠራርጎ ለማስወጣት የተቀጣጠለውን ዘመቻ ከፍጻሜ ለማድረስ ከ[[ሱዳን]] ድንበር ወደ [[ኢትዮጵያ]] የዘለቁት [[ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ]]፣ አርበኞችና የ[[ዩናይትድ ኪንግደም|እንግሊዝ]] ጦር፣ በ[[ኦሜድላ]] ላይ አረንጓዴ፣ ቢጫ፣ ቀይ የሆነውንና የይሁዳ አንበሳ ከመሐሉ የሚገኝበት የ[[ኢትዮጵያ]] ሰንደቅ ዓላማን ተከሉ፤ አውለበለቡ።
 
*[[1944|፲፱፻፵፬]] ዓ.ም. ለ[[አዲስ አበባ]] ሕዝብ የውሃ አገልግሎት የሚሰጠው የ[[ገፈርሳ]] ግድብ በ[[ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ]] ተመረቀ።