ከ«ደርግ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
መስመር፡ 1፦
[[image: DergEmblem emblemof the Derg.pngsvg|170px|thumb|right|የኢትዮጵያ ጊዜያዊ ወታደራዊ አስተዳደር ደርግ]]
'''ደርግ''' ከሰኔ 21፣ 1966 እስከ 1979 ዓ.ም. በ[[ኢትዮጵያ]] ሰፍኖ የነበር የ[[ወታደራዊ አገዛዝ]] ስርዓት አይነት ነበር። '''ደርግ''' የሚለው ቃል ከ[[ግዕዝ]] የተወሰደ ሲሆን ትርጓሜውም [[ቡድን]] ወይንም [[ኮሚቴ]] ማለት ነው። ይህን ቃል ለመጀመሪያ ጊዜ ለስርዓቱ መገለጫነት የተጠቀመው ግለሰብ [[ሻለቃ ናደው ዘካሪያስ]] ሲባል ይሄውም ሰኔ 21፣ 1966 ዓ.ም. ነበር<ref>ኮ/ል መንግስቱ ኃይለማርያም፣ ''ትግላችን፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ አብዮታዊ የትግል ታሪክ''፣ ፀሐይ አሳታሚና አከፋፋይ ድርጅት፣ ታህሳስ 2004 ዓ.ም. (ገጽ 152) </ref>። በዚህ ወቅት፣ በ[[አዲስ አበባ]] ከተማ በሚገኘው የ[[አራተኛ እግረኛ ክፍለ ጦር መምሪያ]] ከተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የተውጣጡ መለዮ ለባሾች በ[[የካቲት]] ወር ስለፈነዳው አብዮት ከሰኔ 19 ጀምሮ ውይይት የሚያካሂዱበት ጊዜ የነበር ሲሆን፤ ሻለቃ ናደው የዚህ ኮሚቴ ማስታወቂያ ጉዳይ ሠራተኛ ነበር። ደርግ በዚህ ሁኔታ በዝቅተኛ መኮንኖች (ከኮሎኔል ማዕረግ በታች) ከተመሰረተ በኋላ በዚያው ቀን [[ሻለቃ መንግስቱ ኃይለማርያም]] የደርግ ሊቀመንበር በመሆን ተመርጦ እስከ ስርዓቱ ማብቂያ (1979) ድረስ በዚያ ስልጣን አገልግሏል።