ከ«ታላቁ ሳርጎን» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
→‎ንጉሥ ከመሆኑ በፊት: clearer to match subject
መስመር፡ 9፦
[[ስዕል:Birth of Sargon BM ME K.3401.jpg|200px| right| thumb|የሳርጎን ልደት የሚነግር ጽላት]]
''የሳርጎን ትውፊት'' በተባለው [[ሱመርኛ]] ጽላት<ref>[http://etcsl.orinst.ox.ac.uk/cgi-bin/etcsl.cgi?text=t.2.1.4# ሱመርኛው የሳርጎን ትውፊት] {{en}}</ref> የአባቱ ስም [[ላዕቡም]] ይሰጣል። ''የነገሥታት ዝርዝር'' የሳርጎን አባት የአጸድ ጠባቂ እንደ ነበር ይለናል። በኋላ ዘመን (7ኛው ክፍለ ዘመን ዓክልበ.) በ[[አሦርኛ]] በተጻፈ ትውፊት ዘንድ፣ ሳርጎን «እናቴ ዝቅተኛ ነበረች፤ አባቴንም አላወቅሁም፣ የአባቴም ወንድም በተራራ ይኖራል» ይላል። ግልጽ የሚሆነው ከንጉሣዊ መነሻ አለመሆኑ ነው። የአሦርኛው ሰነድ ደግሞ እንዳለው እናቱ ዲቃላ ማሳደግ ባለመቻሏ በሸምበቆ ቅርጫት ውስጥ በወንዙ ላይ አስቀመጠችውና የመስኖ ቆፋሪ የሆነ ሰው አኪ አገኝቶት አሳደገው። ሳርጎን ያደገበት መንደር «አዙፒራኑ» በ[[ኤፍራጥስ]] ዳር ሲሆን አኪ የአጸዱ ጠባቂ እንዲሆን እንዳስተማረው ይጨምራል።<ref>[http://www.fordham.edu/halsall/ancient/2300sargon1.html አሦርኛው የሳርጎን ትውፊት] {{en}}</ref>
 
ከተራ ክፍል በመወለዱ ምናልባት ''ሻሩ-ኪን''፥ «ዕውነተኛ ንጉሥ»፥ የልደት ስሙ ሳይሆን ዘውድ ከተጫነው የወሰደው ስያሜ ይሆናል የሚያስቡ ሊቃውንት አሉ። በአካድኛው ስሙ ''ሻሩ-ኪን'' ሲሆን «ሳርጎን» የሚለው አጻጻፍ በ''[[ትንቢተ ኢሳይያስ]]'' ሞክሼው የአሦር ንጉሥ [[2 ሳርጎን]] በዕብራይስጡ እንዲህ ስለሚባል ነው።
 
ሱመርኛው ''የሳርጎን ትውፊት'' ንጉሥ ከመሆኑ በፊት ያለውን ታሪክ እንዲህ ይሰጣል። ሳርጎን ከ[[ኪሽ]] ንጉሥ [[ኡር-ዛባባ]] ሎሌዎች መካከል የቤተ መንግሥት አስረካቢ ሲሆን፣ ንጉሡ ኡር-ዛባባ ሕልምን አይቶ ሳርጎንን የ«ዋንጫ ተሸካሚ» ማዕረግ ሾመው፣ ይህም በመጠጦች (ጠጅ) ሳጥን ላይ ሓላፊነቱን ያለው ማለት ነው። ከዚያ ሳርጎን በራሱ ሕልም ኡር-ዛባባ በደም ወንዝ ውስጥ ሲሰመጥ ያያል። ስለዚህ ኡር-ዛባባ ሰምቶ እጅግ ተቸግሮ ሳርጎንን በተንኮል ለመግደል ያቅዳል። ሳርጎን የንጉሥ ተልዕኮ ሆኖ አንድ መልዕክት በሸክላ ጽላት ለ[[ኡሩክ]] ንጉሥ [[ሉጋል-ዛገሢ]] እንዲወስደው ታዘዘ። መልዕክቱ ግን መልዕክተኛውን ስለ መግደል የሚል ልመና ነበር። ሰነዱ ተሰብሮ ከዚያ በኋላ ምን እንደ ሆነ ቢያጣም፣ ሳርጎን የአካድ መንግሥት መሥራች ለመሆን ስለ በቃ ሴራው እንዳልተከናወነ መገመት እንችላለን።
 
''የነገሥታት ዝርዝሩ''ና ''[[የባቢሎን መቅደስ ዜና መዋዕል]]'' (ወይም «የቫይድነር ዜና መዋዕል» <ref>[http://www.livius.org/cg-cm/chronicles/abc19/weidner.html ABC19]</ref>) የተባለው ጽላት ሳርጎን የኡር-ዛባባ «ዋንጫ ተሸካሚ» በማድረጋቸው ከሱመርኛው ''ሳርጎን ትውፊት'' ጋራ ይስማማሉ። ዜና መዋዕሉ እንዲህ አለው፦ ''ኡር-ዛባባ ዋንጫ ተሸካሚውን ሳርጎንን የመቅደሱን ወይን ጠጅ መሥዋዕት እንዲቀይር አዘዘው። አልቀየረም ግን ለመቅደሱ ቶሎ እንዲሠዋ ጠነቀቀ።'' ከዚህ በኋላ በአረመኔው ጣኦት ሜሮዳክ ሞገስ የዓለም 4 ሩቦች ግዛት እንዳገኘው በማለት ይጨምራል። ይህ ማለት በ[[ኒፑር]] የነበሩት ቄሳውንት ንጉሥነቱን እንዳዳገፉት ይሆናል።
 
ከተራ ክፍል በመወለዱ ምናልባት ''ሻሩ-ኪን''፥ «ዕውነተኛ ንጉሥ»፥ የልደት ስሙ ሳይሆን ዘውድ ከተጫነው የወሰደው ስያሜ ይሆናል የሚያስቡ ሊቃውንት አሉ። በአካድኛው ስሙ ''ሻሩ-ኪን'' ሲሆን «ሳርጎን» የሚለው አጻጻፍ በ''[[ትንቢተ ኢሳይያስ]]'' ሞክሼው የአሦር ንጉሥ [[2 ሳርጎን]] በዕብራይስጡ እንዲህ ስለሚባል ነው።
 
==የሳርጎን መንግሥት==