ከ«ታላቁ ሳርጎን» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
መስመር፡ 58፦
ወደ ምዕራብ ስላደረጉት ዘመቻዎች ሌሎች መዝገቦች ይታወቃሉ። በአንዳንድ ጽላት ዘንድ፣ ሳርጎን የ40 ሺህ ወታደሮች ሠራዊት ነበረው። ከሥራዊቱ ጋር [[ደብረ አማና]]ን ተሻገረ፣ ወደ አርዘ ሊባኖስ ደን ደረሱ። ወደ [[ማርዳማን]] አገር (ከስሜን [[ጤግሮስ]] ምዕራብ የነበረ የ[[ሆራውያን]] ክፍላገር) ለመውረር ያቅዳል። ከዚያ አገር የመጣ ተልእኮ ግን እንዲህ ይጠይቃል፦ «በዳርቻው ክፋቶች የሚያድቡበት የ[[አሞራውያን|አሙሩ]] አገር አይደለምን?» ነገር ግን ሳርጎን አይመልስም፣ የ[[ሲሙሩ]]ም ሰዎችና ከብቶች ሁሉ ይዘው ከተማውን አፈራረሰ። ይህ በስሜን መስጴጦምያ የተገኘ የሆራውያን ከተማ-አገር ነበር። አሙሩ እና [[ሱባርቱ]] አገሮች እንደ ያዙ ይላል።<ref>Joan Goodnick Westenholz, ''Legends of the Kings of Akkad: the Texts'', Text 6, 7.</ref>
 
በ[[ኬጥኛ]] የተጻፈው ግጥም ''የውግያ ንጉሥ'' ስለ ሳርጎን ምዕራብ ዘመቻ ነው። ይህ ጽሑፍ በአካድኛ ትርጉም ደግሞ በ[[አሦር]]ና በ[[አማርና ደብዳቤዎች]] መካከል (በ[[ግብጽ]]) ተገኝቷል። ሳርጎን በጥልቅ በ[[ሐቲ]] አገር ([[አናቶሊያ]]) እንደ ዘመተ ይናገራሉ። ጽሁፉ እንደሚተርከው፣ በሐቲ በ[[ካነሽ]] የኖሩት አካዳዊ ነጋዴዎች በ[[ቡሩሻንዳ]] ንጉሥ ኑርዳጋል እንደ ተበደሉ በማለት ሳርጎን በሩቅ መንገድ ከሠራዊቱ ጋር መጥቶ ኑርዳጋልን እንዲቀጣው በሚል ጥያቄ መልእክት አስረዱት። የኑርዳጋል ሰዎች በጸጥታቸው እየኮሩ ዝም ብሎ የሳርጎን ሥራዊት ደረሰና ቶሎ አሸነፋቸው። ሦስት ዓመት በቡሩሻንዳ ቆይተው የከተማውን ግድግዶች ሰበሩ።
በአሦርኛው ትውፊት እንደሚለው፣
 
በአሦርኛው ''ሳርጎን ትውፊት'' እንደሚለው፣
 
: «ለ[...]4 ዓመታት መንግሥቴን ገዛሁት። የጥቁር ራስ ሕዝብ ላይ ገዛሁት፣ ነገሥኩት፤ ታላላቅ ተራሮች በነሐስ መጥረቢያዎች አጠፋሁ። በላይኛ ተራሮች ወጣሁ፣ በታችኛ ተራሮች በኩል ፈነዳሁ። የባሕሩን አገር ሦስት ጊዜ ወረርሁት፣ ድልሙንን ያዝኩ። ወደ ታላቅ ዱር-ኢሉ ወጣሁ። ... ከኔ በኋላ የሚከበር ማናቸውንም ንጉሥ... የጥቁር ራስ ሕዝብ ላይ ይግዛ፣ ይነግስ። ታላላቅ ተራሮች በነሐስ መጥረቢያዎች ያጥፋቸው፤ በላይኛ ተራሮች ይውጣ፣ በታችኛው ተራሮች በኩል ይፈነዳ፤ የባሕሩን አገር ሦስት ጊዜ ይውረር፤ ድልሙንን ይይዝ፣ ወደ ታላቅ ዱር-ኢሉ ይውጣ።»