ከ«መልከ ጼዴቅ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
Content deleted Content added
No edit summary |
+ |
||
መስመር፡ 23፦
ከዚህ በላይ ከመጽሐፍ ቅዱስ ውጭ ስለ መልከ ጼዴቅ የተለያዩ ትምህርቶችና ታሪኮች አሉ።
*''[[ኪታብ አል-ማጋል]]'' በ[[ቅሌምንጦስ ሥነ ጽሑፍ]] ውስጥ ይመደባል። በዚህ ጹሑፍ ዘንድ፣ [[ሰብአ ሠገል]] ብራናውን ለክርስቶስ በሕጻንነቱ እንደ ስጦታ ሰጡት፣ እሱም ለ[[ጴጥሮስ]]፣ ጴጥሮስም ለተከታዩ ለሮሜ 2ኛው [[ፓፓ]] ለ[[ቅሌምንጦስ]] ያቀረበው ታሪክ ነው። በዚህ መሠረት፣ የመልከ ጼዴቅ አባት የ[[አርፋክስድ]] ልጅ ማሊኽ እንደ ነበር እናቱም ዮጻዳቅ እንደ ተባለች የአርፋክስድ አባት ሴም በጻፈው መዝገብ እንደ ተገኘ ይጨምራል። ከዚህ በላይ፣ በ[[ኖህ]] ትዕዛዝ ሴምና መልከ ጼዴቅ አብረው ወደ [[አራራት]] ሔደው የ[[አዳም]]ን ሬሳ ከ[[ኖህ መርከብ]] አወጡት። ከዚያ በሗላ፣ በመላዕክት ዕርዳታ ወደ ኢየሩስሌም ዞረው በ[[ጎልጎታ]] ኮረብታ ውስጥ አቀበሩት። አብራም በእግዚአብሔር ትዕዛዝ [[ይስሐቅ]]ን እንደ መሥዋዕት ወደ መሥዊያ ቦታ ባመጣው ጊዜ፣ የነበሩበት ኮረብታ ጎልጎታ ሲሆን የመልከ
ተመሳሳይ ዝርዝሮች ''[[የመዛግብት ዋሾ]]'' እና ''[[የአዳምና ሕይዋን ትግል ከሠይጣን ጋራ]]'' በተባሉት መጻሕፍት ይገኛሉ። በ''አዳምና ሕይዋን ትግል'' ዘንድ የመልከ ጼዴቅ አባት የ[[አርፋክስድ]] ልጅ [[ቃይንም]] ነው። ''[[መጽሐፈ ንቡ]]'' የሚባለው ጽሑፍ እንደሚለው የቃይንም 2 ልጆች ሻላሕ ([[ሳላ (የኤቦር አባት)|ሳላ]]) እና ማላሕ ሲሆኑ፣ ማላሕ ዮጻዳቅን አግብቶ የመልከ ጼዴቅ ወላጆች ሆኑ።
እነዚህ ምንጮች እንደሚሉን፣ መልከ ጼዴቅ ከሴም ሹመት በኋላ ቆዳ ለባሽ፣ ከጎልጎታ አቅራቢያ መቸም የማይራቅ፣ እንደ [[ናዝራዊ]] ጽጉሩን መቸም ያላቋረጠ ካህን ሆነ። አብራምን መጀመርያ ባገናኘው ጊዜ ግን እግዜር ጥፍሩን እንዲያቋርጥ አዘዘው። 12 ንጉሦቹ በጽድቁና በመልካምነቱ አድንቀው ወደ አገሮቻቸው እንዲመጣ ቢለምኑት ከዚህ መራቅ አልችልም ብሎ እምቢ አላቸው። ስለዚህ በሠፈሩ እየሩሳሌምን የሠሩለት ነው። በኋላም የይስሐቅ ሚስት [[ርብቃ]] ርጉዝ በሆነችበት ሰዓት ሁለት አገራት (ማለት [[ኤዶምና]] [[እስራኤል]]) በማሕፀንሽ አሉ ብሎ የነበየላት መልከ ጼዴቅ እንደ ነበር በነዚህ መጻሕፍት ይነገራል።
<references/>
|