ከ«አክሊሉ ለማ።» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
መስመር፡ 1፦
==ዶ/ር ኣክሊሉ ለማ==
ሺስቶሶሚያሲስ ወይም ቢልሃርዝያ (Bilharziasis) ሺስቶሶማ በሚባሉ የደም ወስፋቶች ደም ውስጥ መገኘት የሚመጣ የሰው በሽታ ነው።ወንድና ሴት ትሎች ተገናኝነው በመጣበቅ የሰው ደም ውስጥ በመኖር ብዙ ሺህ እንቁላሎች ያፈራሉ። እንቁላሎቻቸው ከሽንት ጋር ሲወጡም ደም ሊያሸኑ ይችላሉ። እንቅላሎቹ ከሰገራና ከሽንት ጋር ከሰውነት ወደ ውጪ ከወጡ በኋላ ቀንድ ኣውጣ ውስጥ ገብተው ይራባሉ። ከእዚያም ከቀንድ ኣውጣው ወጥተው ውሃ ውስጥ በመቆየት የሰውን ቆዳ በስተው ወደ ደም ስር ይገባሉ። በሽታው ሰውን የሚይዘው ሰርኬርያ የሚባሉት የትሉ ኣንድ ዓይነት ደረጃ ሰው ሲዋኝ ወይም በባዶ እግሩ ውሃው ውስጥ ሲሄድ ቆዳን በመብሳት ወደ ሰውነት ስለሚገቡ ነው።
 
ዶ/ር ኣክሊሉ ለማ እንዶድ ቀንድ ኣውጣዎችን ለመግደል ስለሚችል በሽታውን ለመቆጣጠር እንደሚራዳ ስለደረሱበት ዕውቅና ተሰጥቷቸዋል። ዶ/ር ኣክሊሉ ስለ እንዶድ ጥቅምና የውሃ ትላትል መግደል ችሎታ በማግኘታቸው በ፲፱፻፷፮ ዓ.ም. እና በ፲፱፻፹፮ ዓ.ም. ከባልደረቦቻቸው ጋር የዩናይትድ እስቴትስ የፈጠራ ባለቤትነት ወይም ፓተንቶች ኣግኝተዋል። የእንዶድ ማዕከልም ኣቋቁመዋል። ስለ እንዶድ ምርምር ለብዙ ዓመታት በኣዲስ ኣበባ ዩኒቨርሲቲ ስላደረጉት ኣስተዋጽዖ “ራይት ላይቭሊሁድ ኣዋርድ” ወይም “Right Livelihood Award” የሚባል ሽልማት በ፲፱፻፹፩ ዓ.ም. ተሰጥቷቸዋል። እንዲሁም ስለ እንዶድ ምርምር ለብዙ ዓመታት ስላደረጉት ኣስተዋጽዖ ዶ/ር ለገሠ ወልደዮሓንስ ከዶ/ር ኣክሊሉ ጋር “ራይት ላይቭሊሁድ ኣዋርድ” የሚባል ዕውቅና በ፲፱፻፹፩ ዓ.ም. ተሰጥቷቸዋል።