ከ«ቦሌ ዓለም አቀፍ ጥያራ ጣቢያ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
መስመር፡ 1፦
[[ስዕል:Haile Selassie I Airport.jpg|thumb|right|የቀድሞው የበረራ ቁጥጥር እና መንገደኛ ማስተናገጂያ ሕንፃዎች]]
[[ስዕል:Addis Abeba Airport b.7.jpg|thumb|right|ቦሌ ዓለም አቀፍ የጥያራ ጣቢያ (አውሮፕላን ማረፊያ)]]
'''ቦሌ ዓለም አቀፍ የጥያራ ጣቢያ (አውሮፕላን ማረፊያ)''' በ[[አዲስ አበባ]] ከተማ በደቡብ-ምሥራቅ አቅጣጫ ከአራዳ በስምንት ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኝ የአገሪቱ ዋና አድማሳዊ የንግድና የግንኙነት በር ነው።
 
ፕሮፌሶር (ዲባቶ) መስፍን አረጋ፣ ቦሌ በኦሮምኛ ቋንቋ ትርጉሙ የሚፈረፈር ወይም የሚሰነጣጠቅ መሬት እንደሆነ ይነግሩናል። እውነትም የአካባቢው ገጸ-ምድር ለአየር ማረፊያ አመቺ ሜዳማ ቢሆንም መሬቱ ግን ረግራጋ እና መረሬ ነው።
 
==በፋሺስት [[ኢጣልያ]] ዘመናት==
ጥያራዎች (አየር ዠበቦች) ወደአገሪቱ መግባት የጀመሩት በ[[ንግሥት ዘውዲቱ]] ዘመን ሲሆን በ[[አዲስ አበባ]] ዙሪያ በጃን ሜዳ እና አቃቂ ያርፉ እንደነበር በታሪክ ተዘግቧል። የመጀመሪያው ቋሚ የአየር ዠበብየጥያራ ጣቢያ ግን የተሠራው በአምሥቱ የፋሺስት ዘመናት ሲሆን [[የካቲት ፳፬]] ቀን [[1928|፲፱፻፳፰]] ዓ/ም [[አክሱም]] አካባቢ ላይ ከነአውሮፕላኑከነጥያራው ተከስክሶ በሞተው አብራሪያቸው፣ “ኢቮ ኦሊቬቲ” “Ivo Olivetti” ስም ሠይመውት የነበረው የልደታ አየርየጥያራ ጣቢያ ነው።
 
በዚሁ በፋሺስት ወረራ ዘመን ‘አላ ሊቶሪያ’ (ALA LITTORIA S.A., R.) የተሰኘው ኩባንያ በአገር ውስጥ ከ[[አዲስ አበባ]] ተነስቶ [[ነገሌ]]ን፤ [[ሞቃዲሾ]]ን፤ [[ድሬ ዳዋ]]ን፤ ጎራኄን፤ [[ጂቡቲ]]ን፤ [[አሰብ]]ን፤ [[ጂማ]]ን፣ [[ጋምቤላ (ከተማ)|ጋምቤላ]]ን [[ደምቢ ዶሎ]]ን፤ [[ጎንደር]]ን [[አስመራ]]ን፤ [[ደሴ]]ን፤ [[ለቀምት]]ን እና [[አሶሳ]]ን የሚያገለግሉ የበረራ መሥመሮች ሲኖረው ከአድማስ ባሻገር ደግሞ ከተማዋን በ[[ካርቱም]]፣ ዋዲ ሃይፋ፤ [[ካይሮ]]፣ [[ቤንጋዚ]] እና ሲራኩሳ አድርጎ ከ[[ሮማ]] ጋር የሚያገናኝ የበረራ መሥመርም ነበረው።
መስመር፡ 12፦
==ከድል በኋላ==
 
ከድል ወዲህ ልደታ አየርጥያራ ጣቢያ፤ የ[[ብሪታኒያ]] ጦር ኃይሎች ሲገለገሉበት ከቆየ በኋላ [[የኢትዮጵያ አየር መንገድ]] [[ታኅሣሥ ፳፩]] ቀን [[1938|፲፱፻፴፰]] ዓ/ም ሲመሠረት ዋና ጣቢያው እዚያው ነበር።
ዳሩ ግን የአየር መንገዱ አገልግሎት እየተስፋፋ ሲመጣና ትላልቅ ጄት አውሮፕላኖች እንደሚያስፈልጉት ግልጽ ሲሆን፣ የልደታ አየር ጣቢያ ብቃት እንደሌለው እና ለጄት አየር ዠበቦችም ማሳረፊያ የማይስማማ መሆኑ ታምኖበት የአማራጭ ሥፍራ ፍለጋ ተጀመረ። የአዲሱንም አየር ጣቢያ ዝርዝር ጥናት እንዲያዘጋጅ ውሉ ለ[[አሜሪካ]]ዊው ‘አማን እና ዊትኒ’ (Amman, and Whitney) ኩባንያ ተሰጥቶ፤ ጥናቱ በ[[1950|፲፱፻፶]] ዓ/ም ተገባዶ አማራጩ ሥፍራ ቦሌ እንዲሆን ተወሰነ።
 
==አዲሱ አየርየጥያራ ጣቢያ==
ቦሌ ሜዳማ አካባቢ ሲሆን፣ ለመነሳትም ሆነ ለማረፍ ከሚከለክሉ ተራራዎችና ጋራዎች የራቀ ሥፍራ ነው። የከተማዋም ወሰን በወቅቱ ከመስቀል አደባባይ እና ከኡራኤል በማያልፈት ጊዜ ለአየር ጣቢያው ቋሚነት የታጨው አካባቢ ከከተማ ውጭ እና ራቅ ያለ ድንግል ልማት ነበር። የአየር ጣቢያውን የግንባታ ወጪ ከ[[አሜሪካ]]ዊው ‘ኤክስፖርት-ኢምፖርት’ ባንክ በተገኘ ብድር ተሸፍኖ ሥራው ተጀመረ።
 
የግንባታው ሥራ ጨርሶ ባይጠናቀቅም እንኳ፤ የማኮቦቢያው እና የበረራ ቁጥጥሩ ሕንፃ ሥራ እንደተገባደደ [[የኢትዮጵያ አየር መንገድ|አየር መንገዱ]] የገዛቸውን ሁለት የጄት ዠበቦች (‘ቦይንግ ፯፻፯) ሲረከብ እዚሁ ቦሌ አየርጥያራ ጣቢያ ነበር ያረፉት። ጠቅላላ ግንባታው ተጠናቆ ሲያልቅ [[ኅዳር ፲፩]] ቀን [[1956|፲፱፻፶፮]] ዓ/ም ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ተብሎ፣ [[ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ|በንጉሠ ነገሥቱ]] ተመርቆ ተከፈተ።
 
==እድሳት እና መስፋፋት==
 
የአዲሶቹ ''ጄት'' አውሮፕላኖችጥያራዎች ክብደት፤ የአየር መንገዱ በረራ መሥመሮች መባዛት እና የማኮብኮቢያው መሠረት ግንባታ ጥንካሬ ወትሮውንም አስተማማኝ አለመሆን፤ የተነጠፈውም መረሬ እና የመሸርሸር ጠባይ ባለው አፈር ላይ በመሆኑ ከአምሥት እና ስድስት ዓመታት አገልግሎት በኋላ የመሰነጣጠቅ ባህሪ ይታይበት ዠመር። ስለዚህ ማኮብኮቢያውን የማጠንከር እና ርዝመቱን በ ሰባት መቶ ሜትር የማራዘም ሥራ አዲስ በተገኘ ብድር ተጠናቋል።
 
የአገሪቱ የአየር ግልጋሎት እያደገ ሲሄድ መንገደኛ ማስተናገጃ ሕንፃዎቹም የግድ መስፋፋት እንደነበረባቸው ግልጽ ሲሆን ከ[[ጃፓን]] መንግሥት በተገኘ ብድር ተስፋፍቶ [[ኅዳር ፳፩]] ቀን [[1970|፲፱፻፸]] ዓ/ም ተመርቆ ተከፈተ።