ከ«ቅኔ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
Content deleted Content added
No edit summary |
No edit summary |
||
መስመር፡ 1፦
'''ቅኔ''' ማለት፡ 'ቀነየ' ፡ገዛ፡ ካለው፡ ግስ፡ የተገኘ፡ ጥሬ፡ ዘር፡ ነው። ወይም፡ 'ቀነየ' ፡ገዛ፡ የሚለውን፡ አንቀጽ፡ ያስገኘ፡ ጥሬ፡ ዘር፡ ነው። ፍችውም፡ 'መገዛት'፡ ማለት፡ ነው። 'ቁሙ፡ እንከ፡ ወኢትሑሩ፡ ዳግመ፡ ውስተ፡ አርዑተ፡ ቅኔ'፡ እንዲል፡ (ገላ.፥5፥1)፥ ቅኔ፡ ማለት፡ መገዛት፡ ማለት፡ ከኾነ፥ ይህ፡ ከያንዳንዱ፡ ሰው፡ በየጊዜው፡ የሚመነጨው፡ እንግዳ፡ ድርሰት፡ ስለ፡ ምን፡ ቅኔ፡ ተባለ፡ ቢሉ፥ ፍጡር፡ ዐዲስ፡ ዐዲስ፡ ምስጋና፡ እየደረሰ፡ በማቅረብ፥ ለፈጣሪው፡ መገዛቱን፡ የሚገልጥበት፡ ስለ፡ ኾነ፡ ነው። ለፍጡራን፡ የሚደረሰውም፡ ቅኔ፥ ቅኔው፡ የሚደረስለት፡ ፍጡር፡ ከቅኔ፡ ደራሲው፡ በላይ፡ ክብር፡ ያለው፡ መኾኑን፡ የሚገልጽ ፡ ድርሰት፡ ስለ፡ ኾነ፥ መገዛትን፡ ከማመልከት፡ የራቀ፡ አይደለም።
አንድም፥ ሕዋሳተ፡ አፍኣን፣ ሕዋሳተ፡ ውስጥን፡ ለኅሊና፡ አስገዝቶ፥ በተወሰነ፡ ቍርጥ፡ ሐሳብ ፡ የሚታሰብ፡ ስለ፡ ኾነ፥ ቅኔ፡ ተብሏል። ይኸውም፡ ሊታወቅ፥ በቅኔ፡ ምስጢር፡ ልቡ፡ የተነካ፡ ሰው፥ ቅኔ፡ በሚያስብበት፡ ጊዜ፥ እፊቱ፡ የሚደረገውን፡ ነገር፡ እያየ፣ እየሰማ፥ አይሰማም። ከዚህም፡ የተነሣ፥ በጎንደሮች፡ መንግሥት፥ የቍስቋሙ፡ አለቃ፡ በእልፍኙ፡ ውስጥ፡ ምንጣፉን፡ አስነጥፎ፥ መጻሕፍቱን፡ እፊቱ፡ ደርድሮ፥ ለበዓለ፡ ቍስቋም፡ የሚቀኘውን፡ ቅኔ፡ ሲያወጣና፡ ሲያወርድ፥ ንጉሡ፡ ዘው፡ ብለው፡ ቢገቡ፥ ልቡ፡ ተመሥጦ፥ ሊያያቸው፡ ባለመቻሉ፥ ቀና፡ ብሎ፡ ሳያያቸው ፡ ቁጭ፡ እንዳለ፡ ቀረ። ንጉሡም፥ ነገሩ፡ ደንቋቸው፥ ፍጻሜውን፡ ለማየት፥ ርሱን፡ ዐልፈው፡ ዐልጋ፡ ላይ፡ ተቀምጠው፥ ኹኔታውን፡ ይመለከቱ፡ ዠመር።
ብዙ፡ ሰዓት፡ ካሳለፈ፡ በዃላ፥ አእምሮው፡ ሲመለስ፥ ንጉሡ፡ ተቀምጠው፡ ቢያይ፥ ደንግጦ፡ ተነሥቶ፡ እጅ፡ ነሣ። ንጉሡም፦ ምነው፧ ምን፡ ኾነኽ፡ነው፧ ቢሉት፦ ጃንሆይ፥ ቍስቋምን፡ ያኽል፡ ደብር ፡ አምነው፡ ሾመውኛል፤ ለበዓል፡ የተሰበሰበው፡ ሰው፡ አለቃው፡ ምን፡ ይናገር፡ ይኾን፧ እያለ፡ ዐይን፡ ዐይኔን፡ ሲያየኝ፥ ያልኾነ፡ ነገር፡ ቢሰማ፡ ደብሩን፡ አዋርዳለኹ፥ ጃንሆይንም፡ አሳማለኹ፥ እኔም፡ አፍራለኹ፡ ብዬ፥ ቅኔ፡ እቈጥር፡ ነበር፡ አለ፡ ይባላል።
አንድም፥ ቅኔ፡ ማለት፥ 'ተቀንየ'፡ ሙሾ፡ አወጣ፥ ግጥም፡ ገጠመ፥ አራቆ፡ ተናገረ፥ አዜመ፥ አንጐራጐረ፥ መራ፥ ዘፈነ፡ ካለው፡ የወጣ፡ ጥሬ፡ ዘር፡ ነው። ስለዚህ፥ ቅኔ፡ ማለት፥ ባጪሩ፥ ጠቅላላ፡ ትርጕሙ፥ ሰው፡ ከራሱ፡ አንቅቶ፡ ለእግዚአብሔር፡ ዐዲስ፡ ምስጋና፡ ላቅርብ፡ ባለ፡ ጊዜ፥ ምሳሌ መስሎ፥ ምስጢር፡ አሻሽሎ፡ ግጥም፡ በመግጠም፥ የልቡናውን፡ ዕውቀት፣ የአእምሮውን፡ ርቀት፡ የሚገልጽበት፥ የዕውቀቱን፡ ደረጃ፡ የሚያስታውቅበት፥ የሰሚንም፡ ልቡና፡ የሚያነቃቃበትና፡ የሚያራቅቅበት፡ ድርሰት፡ ማለት፡ ነው። ከዚህም፡ የተነሣ፥ መጋቢ፡ መርሻ፡ ኀይሉ፡ የተባሉ ፡ የዲማው፡ ባለ፡ ቅኔ፦ የሰውን፡ ዕውቀቱን፡ መጠን፡ የማውቀው፡ በቅኔው፡ ነው፡ ይሉ፡ ነበር፡ ይባላል።
ከስም ውስጥ ይተሽሞነምነ ወርቅ እንደሚወጣ ሁሉ ከቃላትም የተደበቀ ምስጢር ሲወጣ ያ ጥበብ [[ሰምና ወርቅ]] ('''ቅኔ''') ይሰኛል።
|