ከ«መርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
መስመር፡ 4፦
በቤተ ክርስቲያን የመጀመሪያ ትምህርታቸውን እስከ ዳዊት ድረስ ካጠናቀቁ በኋላ የዜማ ትምህርት ተከታትለው ጾመ ድጓ እና ድጓን ዘልቀዋል። ቀጥሎም የቅኔ ትምህርታችውን አጠናቀው በ [[1905|፲፱፻፭]] ዓ/ም በአሥራ አራት ዓመት ዕድሜያቸው በወንበር ፀሐፊነት የመጀመሪያ ሥራቸውን ጀመሩ።
 
የመጻሕፍተ ሐዲሳትን ትርጓሜ፤ የዮሐንስ አፈወርቅን ትርጓሜ፤ እንዲሁም የመቅድመ ወንጌልን ትርጓሜ ትምህርት ያጠናቀቁት እኝህ ታላቅ ሰው [[ብርሃንና ሰላም (ጋዜጣ)]] የተሰኘው ጋዜጣ ሲመሠረት የጋዜጣው ዋና አዘጋጅ በመሆን፣ ቀጥለውም በ[[ተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት]] የ[[ግዕዝ]]ና የ[[አማርኛ]] አስተማሪ በመሆን አገልግለዋል። ከፋሺስት ወረራ በኋላ ከ[[1933|፲፱፻፴፫]] ዓ/ም እስከ [[1963|፲፱፻፷፫]] ዓ/ም ድረስ በተለያዩ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች በኃላፊነትና በ ዲሬክቶርነት ሲያገለግሉ ቆይተዋል።
 
ሥነ ጽሑፍንና ታሪክን በተመለከተ፣ አሥራ ሦስት መጻሕፍትን የደረሱ ሲሆን፣ ሰባት መጻሕፍት ደግሞ ተርጉመው አቅርበዋል። እንዲሁም የተለያዩ ጽሑፎችን አሰባስበው ከማዘጋጀታቸው ባሻገር፣ የቅዱሳት መጻሕፍት ሥራዎችም ከሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ጋር በትብብር አዘጋጅተዋል። ብላታ መርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ አንዱ የ[[አማርኛ]] ቋንቋ አባት ተብለው ቢወደሱ ማጋነን አይሆንም። ይህም የተባለበት ምክንያት የአማርኛ ሰዋሰውን አስመልክቶ ባደረጉት ጥልቅ ምርምሮች እና በተቀናጀ መልክ የተዘጋጁ የአማርኛ ሰዋሰው መማርያ መጸሐፍትን በመጻፋቸው ነው። በ[[ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ]] ሽልማት ድርጅት ተቀጥረው በተርጓሚነት፣ በአዘጋጓጅነት እና በደራሲነት ባገለገሉበት ጊዜ ከ፴፭ በላይ የሚሆኑ መጽሐፍትን ለህትመት እንዲበቁ አድርገዋል። በዚህም መሰረት የአማርኛን ቋንቋ ከዘመናዊ እና ከኪነታዊ አነጋገር በማስማማት ላደረጉት የላቀ አገልግሎት ድርጅቱ በ[[1964|፲፱፻፷፬]] ዓ.ም. የአማርኛ ሥነ-ጽሑፍ ሽልማትን ሰጥቷቸዋል። ከዚህም በተጨማሪ እንደ መምህር፣ ርዕሰ-መምህር ከማገልገላቸውም ባሻገር በብሪታንያ-ሶማሌላንድ እና በፈረንሳይ-ሶማሌንድ መካከል የተፈጠረውን የድንበር ግጭት ለመፍታት ለሦስት ዓመታት (ከ[[1924|፲፱፻፳፬]] እስከ [[1927|፲፱፻፳፯]] ዓ/ም) ያገለገለው ኮሚሽን አባል እና ዋና ፀሐፊ በመሆን አገልግለዋል። የከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኛ፤ የሕግ ምክር ቤት ምክትል ፕሬዘዳንት እና አማካሪ በመሆንም ለሀገራቸው ሰርተዋል። ከለይ ከተጠቀሱትም ባሻገር የኢትዮዽያን ታሪክ በማጥናትና [[መጽሐፍ ቅዱስ]]ን ወደ አማርኛ በመተርጎም ሥራ ላይ ያላሰለሰ አስተዋጽኦ አድርገዋል።