ከ«ኅሩይ ወልደሥላሴ (ብላቴን ጌታ)» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
r2.7.1) (ሎሌ መጨመር: pl:Hyruj Uelde Syllasje
No edit summary
መስመር፡ 1፦
[[Image:Heruyjapan2.jpg|right|thumb|300px]]
[[ስዕል:Blaten-Geta Heruy.JPG|right|thumb|200px|የብላቴን ጌታ ኅሩይን ሞት የሚያበሥር ደብዳቤ]]
'''ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴ''' በ[[ኢትዮጵያ]] መኻል አገር በሰሜን [[ሸዋ]] [[በመርሐ ቤቴ]] አውራጃ በታች ቤት ወረዳ ረመሸት ቀበሌ ደን አቦ ገዳም በተባለ ሥፍራ በ [[1871|፲፰፻፸፩]] ዓ.ም ተወለዱ። ሲወለዱ የተሰጣቸው ስም ገብረመስቀል ነበር። በቤተ ክህነት ትምህርት እንጦጦ ራጉኤል ደብር መጥተው የመጻሕፍትን ትርጓሜ በዘመኑ ከነበሩት የደብሩ ሊቃውንት ዘንድ ተምረው አጠናቀዋል። እዚህ ነው አንዱ መምህራቸው «አንተ የቀለም ቀንድ ስለሆንክና በምግባርህም የተመሰገንህ ነህና፡ ኅሩይ የተባለውን ስሜን ሸልሜያሃለሁ፡ ከንግዲህ ኅሩይ እየተባልክ ተጠራ!» አሏቸው። <ref>''የኢትዮጵያ ታሪክ፡ ከንግሥተ ሳባ እስከ ታላቁ የአድዋ ድል'' በብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴ - [[1999|፲፱፻፺፱]] ዓ.ም</ref>
 
ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴ ሃያ አንድ መጻሕትንመጻሕፍትን የደረሱ ሲሆኑ፤ የመጨረሻው መጽሐፋቸው ''«የኢትዮጵያ ታሪክ፡ ከንግሥተ ሳባ እስከ ታላቁ የአድዋ ድል''» ለመጀመሪያ ጊዜ በ [[1999|፲፱፻፺፱]] ዓ.ም የልጅ ልጃቸው ወይዘሮ ሠናይት ተክለማርያም አሳተሙት። ደራሲው ፋሽሽት [[ኢጣልያ]] ኢትዮጵያን በወረረ ጊዜ ከ[[ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ]] ጋር አብረው ወደ [[እንግሊዝ]] አገር ስደት ላይ እንዳሉ በ ስልሳበስልሳ ዓመታቸው [[መስከረም 9|መስከረም ፱]] ቀን [[1931|፲፱፻፴፩]] ዓ.ም. አረፉ።
 
ሥርዓተ ቀብራቸው [[መስከረም 10|መስከረም ፲]] ቀን እዚያው እንግሊዝ አገር ሲፈጸም ንጉሠ ነገሥቱ የሚከተለውን ንግግር አደረጉ።
<blockquote>
"«አሁን የአዳምን ልጆች ወግ ሲቀበል የምታዩት ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴ በአገራችን ሥርዓት በመልካም አያያዝ ያደገ ከኢትዮጵያም ከፍ ካሉት ሊቃውንት የሚቆጠር ነው። ብልሃቱንና ትጋቱንም ለመልካም ሥራ የሚያገለግሉ መሣሪያዎች ስላደረጋቸው በመንግሥታችን ሥራ ለመመረጥና ወደ ታላቁ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት ለመድረስ በቃ። በየጊዜው የጻፋቸው ከፈትኛ ባህሪውን የሚገልጹ መጻሕፍት፤ ይልቁንም በቤተ ክህነትና በታሪክ እውቀት በዓለም ሊቃውንት ዘንድ የታወቀና የተከበረ አደረጉት። ለምታውቁት ሰው ከታሪኩ ከዚህ የበለጠ ልነግራችሁ የሚያስፈለግ አልመሰለኝም።
 
በአጭሩ ከጠባዩ ትልቅነት የሚሰማኝን ለመናገር ሳስብ ጊዜውን ሁሉ ቁም ነገር በመሥራት ማሳለፉ፤ ከራሱ ይልቅ የተቸገሩትን ለመርዳት መጣሩ፤ እውነትን፣ ፍርድንም ማክበሩና በአገር ፍቅር መቃጠሉ ትዝ ይሉኛል።
መስመር፡ 15፦
በክፉ አድራጊዎች የሚገፋ የዓለምን ፀጥታ የሚያናውጥ ነፋስ ምንም ቢያንገላታህና በታላቅ ፈተና ላይ ቢጥልህም ሊያሸንፍ አልቻለም። ታላቅና ቸር በሆነው ጌታ በተመደበው ሕግ ግን መታዘዝ ግድ ሆነብህ። ይህም ለያንዳንዳችን የሚደርሰን ዕድል ነው። አንተም እስከ መጨረሻ ከታገልክ በኋላ ዛሬ ደከመህ፣ አንቀላፋህም። በሥጋ ብትለየንም ስምህና ሥራህ በመካከላችን ይኖራሉ።
 
ኅሩይ! እግዚአብሔር ሲያስበን አጥንቶችህና መንፈስህ የሚሰፍሩበትን ቦታ እስኪያዩና ከአባቶችህ እስኪቀላቀሉ ድረስ በእንግድነት በመጣህበት በዚህ ሥፍራ በሰላም ዕረፍ።"» <ref>''የኢትዮጵያ ታሪክ፡ ከንግሥተ ሳባ እስከ ታላቁ የአድዋ ድል'' በብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴ - ፲፱፻፺፱ (1999) ዓ.ም </ref>
</blockquote>