ከ«አማራ (ክልል)» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
r2.7.2+) (ሎሌ ማስተካከል: es:Región de Amhara
No edit summary
መስመር፡ 1፦
[[ስዕል:Ethiopia-Amhara.png|thumb|200px|አማራ ክልል]]
'''አማራ''' (ክልል 3) ከዘጠኙ የ[[ኢትዮጵያ]] ክልሎች አንዱ ነው። ዋና ከተማ [[ባሕር-ዳር]] ነው። የአማራ ብሔራዊ ክልል ጅኦግራፊያዊ አቀማመጥ በ8° 45 እስከ 13° 45 ሰሜን የኬንትሮስ እና በ35° 46 እስከ 40° 25 ምስራቅ የኬንትሮስ መስመር ውስጥ የሚገኝ ሲሆን በምስራቅ የ[[አፋር (ክልል)|አፋር]]ና የ[[ኦሮሚያ ክልል|ኦሮሚያ]] ክልሎች፣ በምዕራብ [[ሱዳን]] እና [[ቤንሻንጉል-ጉምዝ ክልል]]፣ በሰሜን የ[[ትግራይ ክልል]]ና በደቡብ የኦሮሚያ ክልል ያዋስኑታል፡፡ የቆዳ ስፋቱ ፻፶፯ሺ፸፮ ካሬ ሜትር ሲሆን ከአገሪቱ አሥራ አምስት በመቶ ድርሻ ይይዛል፡፡የየክልሉ ሕዝብ ብዛት ደግሞ በ[[2ዐዐ2|፳፻፪]] ዓ/ም ፲፰ ሚሊዮን ፻፺፪ ሺ ፯መቶ ፺፭ እንደነበር የተገመተ ሲሆን ከአገሪቱ ጠቅላላ ሕዝብ ሩብ እጅ አካባቢ ድርሻ ይይዛል፡፡
'''አማራ''' (ክልል 3) ከዘጠኙ የ[[ኢትዮጵያ]] ክልሎች አንዱ ነው። ዋና ከተማ [[ባሕር-ዳር]] ነው። 156,960 ካሬ ኪ.ሜ. የሚሆን የቦታ ስፋት ሲኖረው የሕዝብ ብዛት ደግሞ (በ[[1991]]) 19,120,005 ነው። ክልሉ አራት ዞኖች ሲኖሩት፣ እነርሱም፤
 
ክልሉ በ፲ ዞኖችና በ፻፷፮ የገጠርና የከተማ ወረዳ አስተዳደሮች የተከፋፈለ ሲሆን ከዚህ ውስጥ ፴፰ የሚሆኑት የከተማ አስተዳደሮች ናቸው፡፡የአማራ፣የአገው፣የኦሮሞና የሌሎች ብሔረሰቦች በጋራ የሚኖሩበት ክልል ነው፡፡ በዚሁ ክልል ውስጥ [[ሰሜን ሸዋ]] አንዱ የአማራ ክልል እና ባለታሪክ ክልል ሲሆን የ[[አጼ ሚኒሊክ]] የትውልድ ሀገር ከ[[ደብረብርሃን]] 5 ኪሎሜትር ርቀት [[አንጎለላ]] አካባቢ ሲሆን ይህ ክልል በጀግንነት የሚታወቅ ቦታ ነው። ከእነሱም ውስጥ [[ተጉለት]] ፣[[ቡልጋ]] ፣ [[ምንጃር]] ፣ [[ጅሩ]] ፣[[መሬ]]/[[መርሀቤቴ]]/ ፣ [[መንዝ]] ፣ [[ይፋት]] ፣ [[አንኮበር]] ፣እና ሌሎችም አሉ። ይሄ ዞን ጀግንነት ብቻ ሳይሆን ደግነትና እንግዳ ተቀባይ ፣ አክባሪ ፣ ሀይማኖተኛ ፣ፈሪሀ እግዚአብሔር በልቡ ውስጥ ያለው ፣ አትንኩኝ ባይ ፣ ጀግና ሕዝብ ነው። ይህ ክልል 98.5 በመቶ [[አማርኛ]] ቋንቋ ተናጋሪ ነው ። ነገር ግን ጥንቱ የ ቤተ አምሐራ ምድር መነሻ የ አሁኑንየአሁኑን [[ወሎ]] አጠቃሎ የያዘ ሲሆን በውስጡም ጥንታዊውን አምሐራ ሳይንት፣ ደብረሲና፣ ተንታ፣ወግዲ፣ከለላ፣ለጋንቦ፣ኩታበር፣አምባሰል፣ሮሃ(ላሊበላ)፣ደላንት፣ደላንታ እና ዳውንት፣ግዳን...ወዘተ ያጠቃልላል።
 
ሌላው ያአማራ ክልል ዞን [[ሰሜን ጎንደር]] ነው። ዞኑ ከ20 በላይ ወረዳዎች ሲኖሩት ብዙ ታሪካዊ ቦታዎች ይገኛሉ። ከነዚህም መካከል [[የፋሲል ግንብ]] ፣[[የሲስኒዮስየሱሰንዮስ በተ መንግስት]]፣ [[የዞዝ አምባ ውቅር ፍልፍል ገዳም]]፣ ዋሻ ፣ [[የጎርጎራ ወደብ]]፣ [[የወርቃምባ ውቅር ፍልፍል በተ ጊዎርጊስ ገዳም]]... የ[[ራስ ዳሸን]] ተራራ ወዘተ. ናቸዉ።
በአማራ ክልል ዉስጥ 11 ዞኖች ሲገኙ ከነዚህ ዉስጥ [[ሰሜን ጎንደር]] አንዱ ነው።
ዞኑ ከ20 በላይ ወረዳዎች ሲኖሩት ብዙ ታሪካዊ ቦታዎች ይገኛሉ። ከነዚህም መካከል
[[የፋሲል ግንብ]] ፣[[የሲስኒዮስ በተ መንግስት]]፣ [[የዞዝ አምባ ውቅር ፍልፍል ገዳም]]፣ ዋሻ ፣ [[የጎርጎራ ወደብ]]፣ [[የወርቃምባ ውቅር ፍልፍል በተ ጊዎርጊስ ገዳም]]... የ[[ራስ ዳሸን]] ተራራ ወዘተ. ናቸዉ።
 
[[ምዕ/ጎጃም ዞን]]ም በዚሁ ክልል ውስጥ የሚገኝ ሲሆን በውስጡ ቡሬ ወምበርማ ወረዳ፡ ሰከላ፡ ይልማና ደንሳ፡ [[ደምበጫ]]ና [[ዳሞት]] ወረዳዎችን ይገኙበታል። ቡሬ ወረዳ የንግድ ማኣከል ስትሆን [[ወለጋ]]ን ([[ነቀምት]]ን)፡ [[አዲስ አበባ]]ን አና [[ባህር ዳር]]ን ታገናኛለች። በወረዳዋ ዉስጥ ሁሉም አዝዕርቶች የሚመረቱ ቢሆንም በዋናነት [[በርበሬ]]፡ [[ጤፍ]]፡ [[በቆሎ]]፡ በብዛት ይመረታሉ። ቡሬ ወረዳ አንድ ግብርና ማሰልጠኛ፡ አንድ ሀይስኩል፡የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት፡ 1 ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ፡ 1 ፕሪፓራቶሪ አና 3 አንደኛና መለስተኛ ት/ቤቶች ይገኙባታል። የማዕድን ዉሃ ፋብሪካና ሌሎች የግብርና ማቀነባበሪያዎችም ይገኛሉ። ለግብርና ኢንቨስትመንት ምቹ የሆነ የአየር ንብረትና መሬት ያላት ወረዳ ስትሆን ባለሃብቶች በዚህ አካባቢ ቢሰማሩ ዕራሳቸዉን ጠቅመቅው ህብረተሰቡን መጥቀም ይችላሉ።
 
=የተፈጥሮ ሀብት=
በመስህብ ደረጃ በአካባቢዉ ብዙ ታሪካዊ ገዳማትና ለቱሪስት መስህብ ኢሂኑ ሚችሉ ቦታዎች ቢኖሩም ብዙም የታወቁና ለቱሪስት የተዋወቁ አይደሉም። ለምሳሌ ፦ አደል ሚካዒል፡ ይስር ፋፋቴ፡ ባንጃ ተራራው ወዘተ...
በክልሉ አልፎ አልፎ ከሚታዩ የመንግሥትና የማኅበራት ደኖች፣ በደሴቶች፣በአብያተ ክርስቲያናት፣ በወንዞች ዳርቻና ሰው ሊደርስባቸው በማይችሉ ገደላማና ተራራማ ስፍራዎች ከሚገኙ ጥቂት ደኖች በስተቀር ሊጠቀስ የሚችል ከፍተኛ የደን ሀብት ጋር በቅርብ የተያያዘ ነው። በዚህ ረገድ በሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ የሚገኙ እንደ [[ቀይ ቀበሮ]]፣ [[ዋልያ]]፣ [[ጭላዳ ዝንጀሮ]] እንዲሁም በምዕራባዊው የክልሉ አካባቢ [[ዝሆን]] [[አንበሳ]]ና [[ነብር]]፣ [[ሰጐን]]ና የተለያዩ አዕዋፋት በስተቀር ከፍተኛ የዱር እንስሳት ክምችት ካለመኖሩም በላይ በተለያዩ አካባቢዎች ባሉ ጥቂት የደን ቅሪቶችና ዋሻዎች የነበሩት አነስተኛ ቁጥር ያላቸው አራዊቶችም ለዘመናት በደረሰው የደን መጨፍጨፍና መራቆት ምክንያት ከክልሉ ወደ ሌላ አካባቢ እንደተሰደዱ ይታወቃል፡፡
በአሁኑ ወቅት ክልሉ በ11 ዞኖች ተዋቅሯል
 
የክልሉን የማዕድን ሀብት አስመልክቶ በሚገባ የተጠናከረ ጥናት ባይኖርም ከክልሉ ስነ-ምድራዊ ሁኔታዎችና ከተካሄዱ አንዳንድ ጠቋሚ ጥናቶች መረዳት እንደሚቻለው በክልሉ ውስጥ የተለያዩ ማዕድናት እንደአሉ ይገመታል። በዚህም መሠረት በ[[ሰሜን ሸዋ]] የኦፓል ማዕድን፣ በ[[ሰሜን ጐንደር]]፣ በ[[ጭልጋ]]ና በ[[ደቡብ ወሎ]] በ[[አምባሰል ወረዳ]] የድንጋይ ከሰል ክምችት እንዳሉ መረጃዎች ይጠቁማሉ። ከዚህም በተጨማሪ ለግንባታ ሥራ የሚውል በቂ የድንጋይ፣ የኖራ ድንጋይ፣የሸክላ አፈር፣ ጅኘሲየም፣ የጌጣጌጥ ማዕድናት እንዲሁም በዓባይ ሸለቆ የዕብነ በረድ ሐብቶች እንዳሉ ጥናቶች ይጠቁማሉ። ይሁን እንጅ በውል የሚታወቀው ሐብትም ቢሆን በበቂ ሁኔታ አልለማም።
 
=የውሐ ሀብት=
ክልሉ የትልልቅ ወንዞች ባለቤት ሲሆን በአጠቃላይ በሦስት ዋና ዋና ተፋሰሶች ተከፋፍሎ ሊታይ የሚችል ነው። እነርሱም የ[[ዓባይ]]፣ የ[[ተከዜ]] እና የ[[አዋሽ]] ተፋሰስ ናቸው። ወደነዚህ ተፋሰሶች የሚገቡና ዓመቱን በሙሉ የማይደርቁ ቁጥራቸው በርካታ የሆኑ ትልልቅ ወንዞች ያሉ ሲሆን በክልሉ በጥቅም ላይ ያልዋለ ሰፊ የውሐ ሀብት መኖሩን ያመለክታሉ። ከነዚህ በተጨማሪ እንደ ጣናና አርዲቦ የመሳሰሉ ሐይቆችም በክልሉ ውስጥ ይገኛሉ። በአጠቃላይ በክልሉ ውስጥ ባሉ ትልልቅ ወንዞችና መጋቢ ወንዞች የመስኖ ልማት ለማካሄድ የሚያስችል ከፍተኛ የውሐ ሐብት ክምችት እንዳለ መገንዘብ ይቻላል። ይሁን እንጅ እስከ አሁን ጥቅም ላይ የዋለው በጣም አነስተኛ ነው።
 
=ምጣኔ ሀብት=
በአመዛኙ አብዛኛው የክልሉ ምጣኔ ሀብት በግብርና እና ከብት እርባታ ላይ የተመሠረተ ነው። በአጠቃላይ ክልሉ ከፍተኛ የሆነ የሕዝብ ቁጥር፣ ለእርሻና ለእንስሳት እርባታ ተስማሚ የሆነ መሬት፣ የአየር ንብረት እና የውሐ ሀብቶች ያሉት በመሆኑ በተለይም የሰብል እና የእንስሳት ሀብት ልማት ለማካሄድ የማይናቅ አቅም አለው። በዝናብም ሆነ የመስኖ እርሻ ልማት በማስፋፋት በክልሉ በገበያ የሚውሉ የተለያዩ የአገዳ፣ የጥራጥሬ፣ የቅባት፣የአትክልትና ፍራፍሬ ሰብሎችን ማምረት ይቻላል። ጤፍ፣ ገብስ፣በቆሎ፣ ማሽላ፣ዳጉሣ፣ ስንዴ፣አተር፣ ባቄላ፣ ሽምብራ፣ ጓያ፣ምስር፣ሰሊጥ፣ ጥጥ፣ ተልባ፣ ወዘተ የመሳሰሉት በክልሉ ውስጥ ከሚመረቱ ሰብሎች መካከል ዋና ዋናዎቹ ናቸው። በእንስሳት ሀብት ረገድም በወተት ምርታማነታቸው የታወቁ የፎገራ ዝርያዎችና በፀጉር ምርት የታወቁት የመንዝ በግ ዝርያዎች በክልሉ ይገኛሉ።
 
=የጎብኚዎች መስሕብ=
በቱሪዝም የሥራ መስክ ሊበለጽጉ ፣በሰፊው አገልግሎት ሊሰጡ የሚችሉ እና በዓለም የቅርስ መዝገብ የሰፈሩት የጐንደር ቤተ መንስግት ህንፃዎች፣ የ[[ላሊበላ]] አብያተ ክርስቲያናት፣ የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ እንዲሁም ልዩ ልዩ የቱሪዝም መስሕቦች አሉት፣ ይሁን እንጅ ክልሉ ሰፊ የሆነ የቱሪዝም እምቅ ሀብት ያለው ቢሆንም በሚፈለገው መጠን በጥቅም ላይ ውሏል ማለት አያስደፍርም። በዚህ ረገድ፤አካባቢዉ የብዙ ታሪካዊ ገዳማትና የታሪካዊ ቅርሶችም ባለሀብት ነው። ለምሳሌ ከሚጠቀሱት መኃል ፦ አደል ሚካኤል፡ ይስር ፏፏቴ፡ ባንጃ ተራራው ወዘተ...
 
=ዋቢ ምንጭ=
በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ድረ-ገጽ፤ "የክልሉ አጠቃላይ ገጽታ" (accessed 21 Dec 2012)
http://www.amharainfo.gov.et/index.html/index.php?option=com_content&view=article&id=61%3A2011-02-10-05-51-55&catid=7%3Aoverview-of-the-region&Itemid=29&lang=en
 
{{የኢትዮጵያ_መረጃ}}